Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, June 14, 2019

የጠ/ሚ አብይ አህመድ መንግስት በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ የሚያካሂደውን አፈና በጽኑ እናወግዛለን



Addis Ababa police interapted press conference.
የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ መንግስት ከዚህ ቀደም በጋዜጠኛ/የመብት ተሟጋች እስክንድር ነጋ የሚመራው የባለአደራ ምክርቤት በራስ ሆቴል ሊያካሂድ የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ በህገወጥ መንገድ እንዲታገድ አድርጓል። በተመሳሳይ እስክንድር ነጋ የሚገኝበት ሰናይ መልቲ ሚዲያን የተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰኞ ግንቦት 26 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሆቴል በተያዘለት ፕሮግራም መሰረት እንዳይካሄድ ፖሊስ በስፍራው ተገኝቶ ክልከላ አድርጓል።
ይህ በእስክንድር ነጋ ላይ ያነጣጠረ መንግስታዊ የማፈን ተግባር ምንም አይነት ህጋዊ መሰረት የሌለውና በስልጣን ላይ ባለው መንግስት እየተካሄደ ያለ የመብት ረገጣና ህገወጥ ተግባር በመሆኑ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል።
ይህ በእስክንድር ነጋ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ የሚካሄደው አፈና በዚህ አይነት የሚቀጥል ከሆነ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ነገ ተነገወዲያ አፈናው በሌሎችም ላይ የሚፈጸምና የአምባገነንት ሥርዓት እግር አውጥቶ መራመድ መጀመሩን ማሳያ ነው ብለን እናምናለን።
በመሆኑም ይህን አምባገነናዊ የአፈና ተግባር ማንኛውም ነጻነት ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ዜጋ እንዲያወግዘው ብሎም እንዲታገለው ጥሪ እናስተላልፋለን።

No comments:

Post a Comment

wanted officials