Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, June 26, 2019

"የጋምቢያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ያያ ጃሜ ደፍረውኛል"



የ23 ዓመቷ የቀድሞ የጋምቢያ የቁንጅና ንግሥት፣ ፋቱ ጃሎው በ2015 በቀድሞው የጋምቢያ ፕሬዝዳንት ያያ ጃሜ መደፈሯን ተናገረች።
ይህንን ቃሏን የሰጠቸው ሂውማን ራይትስ ዎች እና ትራያል ኢንተርናሽናል ባደረጉት ምርመራ ፕሬዝዳንት ያያ ጃሜ ፈፀሟቸው በተባለው ጾታዊ ትንኮሳና መደፎሮችን ባጋለጠው ዝርዝር ሪፖርት ላይ ነው።
ፋቱ ጃሎው ፕሬዝዳንቱን ስታገኛቸው የቁንጅና ውድድሩን በበላይነት አሸንፋ የነበረ ሲሆን እድሜዋም 18 ነበር።
ይህንን ውድድር ባሸነፈችበት ወር ፕሬዝዳንቱ እንደ አባት እየመከሩ የተለያዩ ስጦታዎችን እና ገንዘብ እየሰጧት አክለውም ቤተሰቦቿ በሚኖሩበት አካባቢ ውሃ እንዲገባ በማስተባበር ቅርበታቸውን አጠናከሩ።
ፋቱ ጃሎውከዛም ትላለች ፋቱ ለፕሬዝዳንቱ ድጋፍ ለማሰባሰብ በተዘጋጀ በአንድ የእራት ግብዣ ላይ የጋብቻ ጥያቄ አቀረቡላት። ፋቱ ግን ጥያቄውን በመቃወም በእራት ግብዣው ላይ ለመስራት የወሰደቻቸውን ኃላፊነቶችን ሰረዘች።
በ2015 ሰኔ ወር ላይ ግን በፕሬዝዳንቱ ቤተመንግሥት በተካሄደ ሀይማኖታዊ ፕሮግራም ላይ እንድትገኝ ተጠየቀች። ቤተመንግሥቱ እንደደረሰች ግን የተወሰደችው ወደ ፕሬዝዳንቱ የግል መኖሪያ ነው።
"ምን እንደሚፈጠር ግልፅ ነበር" ትላለች ፋቱ፤ ፕሬዝዳንቱ የጠየቁትን እምቢ በማለቷ መናደዳቸውን በማስታወስ።
ከዛም በጥፊ እንደመቷትና መርፌ እንደወጓት ታስታውሳለች። ቀጥሎም ደፈሯት።
ቢቢሲ ያያ ጃሜን በስደት በሚኖሩበት ኢኳቶሪያል ጊኒ ስለቀረበባቸው ክስ ለማነጋገር ሞክሮ ነበር።
የፓርቲያቸው ቃል አቀባይ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ላይ የቀረበውን ክስ በአጠቃላይ ክደዋል።
ቃል አቀባዩ ኡስማን ራምቦ ጃታ ለቢቢሲ በላኩት መግለጫ "እንደፓርቲ እና እንደ ጋምቢያ ህዝብ በቀድሞው ፕሬዝዳንት ላይ በሚቀርቡ መሠረተ ቢስ ውንጀላዎች ተሰላችተናል" ብለዋል።
"የቀድሞው ፕሬዝዳንት ለእንዲህ አይነቱ ውሸትና የጥላቻ ዘመቻ መልስ ለመስጠት ጊዜ የላቸውም። የተከበሩ፣ ፈጣሪያቸውን የሚፈሩ፣ አማኝ ለጋምቢያ ሴቶች ክብር ያላቸው ናቸው" ሲሉ የተናገሩት ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ናቸው።
ጃሎ ለቢቢሲ ፕሬዝዳንቱን ፍርድ አደባባይ ለማቆም እንደምትፈልግ ተናግራለች።
"ይህንን ታሪኬን ለመደበቅ፣ ለማጥፋት ሞክሬያለሁ፤ የታሪኬ አካል እንዳልሆነ ለማድረግ ጥሬያለሁ"
"እውነታው ግን አልቻልኩም፤ አሁን ለመናገር የወሰንኩት ታሪኬን በመናገር ያያ ጃሜ የሰሩትን እንዲሰሙ ስለፈለኩ ነው"
አክላም በጋምቢያ ሀቅና እርቅ አፈላላጊ ኮሚሽን ፊት ቀርባ ለመመስከርም ፈቃደኛ መሆኗን ተናግራለች።
ይህ የሀቅና እርቅ አፈላላጊ ኮሚሽን የተቋቋመው በ2016 በፕሬዝዳንት አዳማ ባሮው ሲሆን በያያ ጃሜ የ22 ዓመት አስተዳደር ወቅት የተጸፀሙ ጥፋቶችን ይመረምራል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials