Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, June 10, 2019

የአፍሪካ ቻምፒዮንስ ሊግ፡ ኤስፔራንስ ዋንጫና ሜዳልያ እንዲመልስ ታዟል

የካዛብላንካ ተጨዋቾች 'ቫር' እንዲታይላቸው ሲማፀኑ ነበር

 አጭር የምስል መግለጫ የካዛብላንካ ተጨዋቾች 'ቫር' እንዲታይላቸው ሲማፀኑ ነበር 
 
የአፍሪካ እግር ኳስ አስተዳዳሪ የሆነው ካፍ የአህጉሪቱ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ድጋሚ እንዲካሄድ አዟል፤ ዋንጫውን ያነሳውን ኤስፔራንስም ዋንጫውን ካነሳበት ያስቀምጥ ብሏል።
በአፍሪካ ክለቦች መካከል የሚደረገው የአፍሪካ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ የዘንድሮው በቱኒዚያው ኤስፔራንስ እና በሞሮኮው ካዛብላንካ መካከል ነበር የተካሄደው።
ጨዋታውን ኤስፔራንሶች 1 - 0 እየመሩ ሳለ ካዛብላንካዎች 1 በማስቆጠር አቻ ይሆናሉ። ነገር ግን የዕለቱ ዳኛ ጎሉን ይሽሩታል። ይህ ይልተዋጠላቸው ካዛብላንካዎች ሜዳውን ለቀው ይወጣሉ።

በዕለቱ ቫር [ረዳት የቪዲዮ ዳኛ] ቢኖርም 'ሲስተሙ' ባለመሥራቱ ምክንያት አጨቃጫቂዋን ጎል ድጋሚ ማየት አልተቻለም።
ዳኛው እስከ 95ኛው ደቂቃ ድረስ ከጠበቁ በኋላ ድሉ የኤስፔራንስ ነው ሲሉ አውጀዋል።
ተበደልን ያሉት ካዛብላንካዎች ፕሬዚዳንት 'የእግር ኳስ ቅሌት ሲሳይ' ሆነናል ሲሉ አማረሩ፤ ካፍም አስቸኳይ ስብሰባ ካደረገ በኋላ 'እውነትም ተበድለዋል' ብሏል።
ካፍ ኤስፔራንስ የወሰደውን ዋንጫ እና ሜዳሊያ ከመለሰ በኋላ ድጋሚ ጨዋታ እንዲካሄድ አዟል፤ ጨዋታው በገለልተኛ ሜዳ ይሁንም ብሏል።

ጨዋታው ለሐምሌ 12 ቀጠሮ ተይዞለታል፤ ከግብፁ የአፍሪካ ዋንጫ በኋላ።
ካፍ በመግለጫው 'የጨዋታ ሕግ እና ደንብ አልተከበረም' ስለዚህ ጨዋታው ድጋሚ ይካሄድ ዘንድ ግድ ነው የሚል አንቀፅ አስፍሯል።
የቢቢሲ ስፖርቱ ማኒ ጃዝሚ ኤስፔራንሶች ለካፍ ድክመት ነው እየተቀጡ ያሉት ይላል፤ ምክንያቱም በዕለቱ ቫር አለመሥራቱ የካፍ ጥፋት እንጂ የባለድሎቹ አልነበረም።

No comments:

Post a Comment

wanted officials