Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, June 13, 2019

ሕወሓትና ሻዕቢያን ለማስታረቅ የፌዴራል መንግሥት ዕርዳታ ተጠየቀ።


ሕወሓትና ሻዕቢያን ለማስታረቅ የፌዴራል መንግሥት ዕርዳታ ተጠየቀ።
የኤርትራ ገዥ ፓርቲ ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ/ሻዕቢያ እና የትግራይን ክልል የሚያስተዳድረውን ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይን/ሕወኋት ለማስታረቅ የፌዴራል መንግሥቱ ዕገዛ ተጠይቋል፡፡
‹‹ዳስ ዕርቂ አሕዋት ውድባት››/የዕርቅ ዳስ በሚል በሴሌብሪቲ ኢቨንትስ ሰኔ 5 ቀን 2011 ዓ.ም በተዘጋጀው የዕርቅ መድረክ፣ ሁለቱን ፓርቲዎች ለማስታረቅ፣ ድርጅቱ ማዕከላዊ መንግሥት ዕገዛ እንዲያደርግለትና ለእንቅስቃሴውም ዕውቅና እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡
በሁለቱ አገሮች መካከል የተፈጠረው ሰላም በሕወሓትና በሻዕቢያ መካከል አለመፈጠሩን የሚናገሩት የሴሊብሪቲ ኢቨንትስ መሥራች ወንድማማቾቹ አቶ አብርሃምና አቶ ሀብቶም ገብረ ሊባኖስ፣ በሁለቱ ድርጅቶች ውስጥ የሚታየው ጥላቻና እልህ የአገርን ደኅንነት ሥጋት ላይ የሚጥሉ ድርጊቶች እስከ መፈጸም መድረሱን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ጉዳዩን አስመልክቶ የተደረጉ ጥናቶችም እንደሚያሳዩት፣ ሕወሓትን ያገለለው የኢትዮጵያና ኤርትራ ዕርቅ በሁለቱ ድርጅቶች መካከል የነበረውን መጠራጠርና ጥላቻ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ እንዲከር ማድረጉንም አስረድተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በአየር ትራንስፖርት መግባትና መውጣት ቢቻልም ድንበር አካባቢ ምንም የተቀየረ ነገር የለም ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ያለው ድባብም እንደ ከዚህ ቀደሙ ሰላምም ጦርነትም የሌለበት እንደሆነ የሚናገሩት ወንድማማቾቹ፣ በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለው እልህ ዕርቁ መሬት እንዳይወርድ እንቅፋት መሆኑን ገልፀዋል ሲል የዘገበው ሪፖርተር ነው።
ዐማራ ሚዲያ ማዕከል/ዐሚማ

No comments:

Post a Comment

wanted officials