Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, June 13, 2019

በአቶ ጌታቸው አሰፋ ላይም ሆነ ሌሎች ላይ እየቀረበ ያለው ክስ ‹‹በዓለም ላይ አሳፋሪ የሚባል›› ነው፡፡

‹‹ሕዝቡ የመገንጠል ስሜት ውስጥ ገብቷል›› ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል
በአቶ ጌታቸው አሰፋ ላይም ሆነ ሌሎች ላይ እየቀረበ ያለው ክስ ‹‹በዓለም ላይ አሳፋሪ የሚባል›› ነው፡፡
አቶ ጌታቸው አሰፋን በሚመለከት እስከ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ድረስ ሊያስጠይቅ የሚችል ጉዳይ አለ፡፡
በመንግስት እውቅና ሆን ተብሎ ህዝቡን ለማስራብና ለማስጠማት መንገድ እንዲዘጋ ተደርጓል፡፡
የትግራይ ሕዝብ ላይ ሆን ተብሎ እየተፈጸመ ባለ የዘር ጥቃት ሕዝቡ ከሥርዓቱ ጋር አብሮ ከመቀጠል ይልቅ መገንጠል ስሜት ውስጥ እንደገባ የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ምክትል ፕሬዚዳንቱ ‘ሕዝቡ በሚደርስበት ዘር ተኮር ጥቃት ከፌዴራልም ሆነ ከክልል መንግሥታት ጋር አብሮ በአንድነት መቆየት ላይ ተስፋ ቆርጧል’ ፤ ‘ሆን ተብሎ በሚፈጸም ጥቃት ሕዝቡ ከዚህ ሥርዓት ጋር አብሮ መቀጠል እንደማይቻል እየገለጸ ነው’ ፤ ‘ከራስህ መንግሥት የማትጠብቀው የዘር ጥቃት ዘመቻ ተከፍቷል’ ብለዋል፡፡
በዘር እና በማንነት ያነጣጠረ ጥቃት በትግራይ ላይ እየተፈጸመ ለመሆኑ ማሳያ ብለው በመካከለኛና በታችኛው የመንግሥት ኃላፊነት ላይ የተመደቡ የትግራይ ተወላጆች በሙሉ በአቅም ማነስ ሰበብ ከስራቸው እንዲሰናበቱ እየተደረጉ ነው ሲሉ ጠቅሰወል፡፡
‹‹በአገር ደረጃ የዕብደት ሥራ እየተሠራ ነው፡፡›› ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ‹‹ሰላም እንዲያስከብር በበላይነት ኃላፊነቱን የወሰደው አካል ሲያበላሽ እኛ እያስተካከልንለት ነው፡፡
የእኛ ሥራ ማቀጣጠል አይደለም፡፡ ከክልላችን በላይ ኃላፊነት ደጋግመን በመውሰድ ሰላም ለማስፈን ችለናል፡፡ ግን ለጥቃትና ለማበጣበጥ ኃይል እየተላከብን ነበር፡፡ ከሕግ ውጪ በሆነ መንገድ ወታደር እየተላከብን ለማበጣበጥ ተሞክሯል፤›› በማለት በፌዴራሉ መንግሥት ላይ ከባድ ወቀሳ ሰንዝረዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ አጎራባች በሆነው የአማራ ክልል የመንግሥት ኃላፊዎችም ሆነ በፌዴራል መንግሥት ዕውቅና የተሰጠው በሚመስል አድራጎት፣ የፌዴራል መንግሥት ንብረት የሆነው አውራ መንገድ እየተዘጋ ጭምር ሕዝብ እንዲራብና እንዲጠማ ለማድረግ ተሞክሯል ብለዋል፡፡ አያይዘውም፣ ‹‹መንገድ እየተዘጋ ሕዝብ ሆን ተብሎ እንዲራብና እንዲጠማ ለማድረግ የሚፈጸም ወንጀልን የአማራ ክልልና የፌዴራል መንግሥት ዝም ማለታቸው ሆን ተብሎ ጫና ለመፍጠር መንግሥት ፈቅዷል እንላለን፡፡ ሕዝብ ላይ ጥቃት ሲፈጸም ዝም ያለው መንግሥት ተጠያቂ ነው›› ብለዋል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር የአቶ ጌታቸው አሰፋን ጉዳይ በተመለከተ ለተነሳላቸው ጥያቄ መጠየቅ ያለበት፣ ያጠፋ ይጠየቅ ካሉ በኋላ፣ ‹‹ደማቅ ፊርማ ያለው ቀላል ፊርማ ያለው የሚባል ነገር የለም፡፡ ብሔሩ ትግራይ ስለሆነ ብቻ ከእየ ኮሚቴው እየተመረጠ የሚታሰር ብዙ ነው፡፡ ሊገመት የማይችል ወደ ታች መውረድ እየታየ ነው፡፡
ይኼ የእኛ መንግሥት ነው እንዴ የሚያስብል ዝቅጠት እየታየ ነው፤›› ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ እንደ መንግሥትና እንደ ሕግ አግባብ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ሆኖ በግሉ ያጠፋ ካለ ‹‹ይንጠልጠል ብያለሁ›› በማለት በሕግ አግባብ የሚወሰድ ዕርምጃን እንደሚደግፉ፣ ሆኖም በአቶ ጌታቸው አሰፋ ላይም ሆነ ሌሎች ላይ እየቀረበ ያለው ክስ ግን ‹‹በዓለም ላይ አሳፋሪ የሚባል›› ሆኖ እንዳገኙት ገልጸዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ሕጋዊና ትክክለኛ ዕርምጃ ቢሆን ኖሮ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጭምር የሚጠየቁበት አግባብ እንደሚኖር፣ ሆኖም በግላቸው አቶ ኃይለ ማርያምም ሆኑ አቶ ጌታቸው፣ እንዲሁም ሌሎች የታሰሩ ሰዎች ለመንግሥትና ለሕዝብ በማገልገላቸው መታሰር እንደማይገባቸው፣ በተጨማሪም ከደኅንነት ሥራ ጋር ከተያያዘ የታሰሩ ሰዎች እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡
ምንጭ – ሪፖርተር

No comments:

Post a Comment

wanted officials