.
ከሁለት አመታት በፊት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የነበረው ባራክ ኦባማ ወደኢትዮጵያ በተጓዘበት ወቅት የወያኔ አመራሮች የእራት ግብዣ በማዘጋጀት ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ ሲያስተላልፉ ሐገር ቤት ካሉ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል በወቅቱ በኢ/ር ይልቃል የሚመራው ሰማያዊ ፓርቲ በእራት ግብዣው ላይ መሳተፍ በንፁሃን ሞት ደም ለተዘጋጀው የፌሽታ ፕሮግራም እንዲዘጋጅ አይደለም የምንታገለው በሚል ኦባማ የተገኘበት የእራት ግብዣ ላይ ሳይሳተፍ ቀረ። በወቅቱ ከኢንጂነር ይልቃል ውጭ የተሳተፉ በርካታ ተፎጋጋሪ ፖለቲከኞች የነበሩ ሲሆን ሆኖም ኢንጂነሩ እንደግርማ ሰይፉ መስሏቸው ለኦባማ በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ ይገኝ ዘንድ የህወሀት ሰዎች መልእክት ላኩ ቆፍጣናው ኢንጂነር ይልቃል ግን ህዝቤን እየገደሉና እያሰቃዩ ከሚገኙ ጋር እንዴት እራት እበላለው በማለት ግብዣውን ሰርዞታል። በወቅቱ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተግባሩን በማድነቅ ብራቮ ኢ/ር ድሮስ እንዴት በግ ከአራጁ ጋር ይውላል ብለው ነበረ።
በወቅቱ ኢ/ር ይልቃል ህዝቡን መርጦ የእራት ግብዣውን በመሰረዙ የቀሩበት ነገሮች







አሁን ላይ ደግሞ የአዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ሹመት ምክንያት በማድረግ በቤተመንግሥት በተዘጋጀ የእራት ግብዣ የተወሰኑ ፖለቲከኞች እና አርቲስቶች ተሳትፈው የነበረ ሲሆን በእራት ግብዣው ላይ በመገኘታቸው ምን እንዳተረፉ እና የእነርሱ እዛ መገኘት በሕዝቡ ነፃነት ትግል ላይ ምን እሴት እንደሚጨምር ቢነግሩን ደስ ይለኛል።
የሰሞኑ የፖለቲከኞቻችን ንግግር እና ተግባርን ለተመለከተ አሁንም ቢሆን ከኢንጂነር ይልቃል፣ ከፕሮፌሰር መረራ እና ከአንዳርጋቸው ፅጌ ጋር ሊነፃፀር የሚችል ፖለቲከኛ የለንም።
No comments:
Post a Comment