(ዘ-ሐበሻ) ቅሊንጦን በማቃጠል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 464 እና 494 በመተላለፍ ተከላከሉ ተብለው በተፈረደባቸው በነጋታው ክሳቸው እንዲደተነሳላቸውና እንደሚለቀቁ የተነገረው እነ ዶክተር ፍቅሩ ማሩ ዛሬ ከ እስር ቤት መውጣታቸው ተዘገበ::
ክስ ተቋርጦላቸዋል ተብሎ ሲነገር የነበረው 62 ተከሳሾች የነበሩ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ምን ያህሉ በዛሬው ዕለት እንደተለቀቁ ለማወቅ አልቻልም:: ሆኖም ግን ከተፈቱት መካከል ዶክተር ፍቅሩ ማሩ; አግባው ሰጠኝ; ሲሳይ ባቱ; ፋሲል አለማየሁ እንዲሁም ከበደ ጨመዳ እንደሚገኙበት ለማረጋገጥ ችለናል::
በእነ ማስረሻ ሰጠኝ መዝገብ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ችሎት ጉዳያቸው ሲታይ ከነበሩት 38 ተከሳሾች ደግሞ፤ አራቱ በሰው መግደል ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው እንዲከላከሉ፤ ስምንቱ ግን በነጻ እንዲሰናበቱ መወሰኑ ይታወሳል።

No comments:
Post a Comment