Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, March 18, 2018

በጎንደር በነዳጅ እጥረት ባጃጆች ችግር ውስጥ ወድቀዋል

 በስኬት እየተካሄደ ባለው የነዳጅ እቀባ አድማ የተነሳ በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የነዳጅ እጥረት ተከስቷል:: በተለይ ቄሮ ያደረገውን ጥሪ ተከትሎ ፋኖ ከመተማ የሚመጡ የነዳጅ ቦቴዎችን ያስቆመ ሲሆን ይህም ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል::
መንግስት የነዳጅ እጥረት በሃገሪቱ እንዳልተከሰተ የነዳጅ ድርጅት ባለስልጣንን አቅርቦ በሚዲያው ሲያስነገር ቢቆይም አርብ ምሽት ለመንግስት ጋዜጠኞች ቃለምልልስ የሰጡት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ በተቃውሞው የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት ምክንያት እንደሆነ ማመናቸው አይዘነጋም::
በዚህም መሰረት በጎንደር ትናንትና እና ዛሬ የሕዝብ ማመላለሻ የሆኑት ባጃጆች በየቦታው ተሰልፈው መቆማቸውን ከስፍራው በፎቶ ግራፍ ተደግፎ የደረሰን መረጃ ያሳያል:

No comments:

Post a Comment

wanted officials