Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, March 25, 2014

የአንድነት ፓርቲ‹‹የእሪታ ቀን››በሚል መሪ ቃል መጋቢት 28/2006 ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደርግ አስታውቀ

AA 001
AA 002
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከተማይቱ መሰረታዊ ችግሮች እየተባባሱ ከመምጣት ውጪ ለውጥ ማሳየት ባለመቻላቸው ለዚህ ተጠያቂ መሆን ያለበትን የከተማይቱን አስተዳደርና ገዢውን ፓርቲ የሚቃወም ‹‹የእሪታ ቀን››በሚል መሪ ቃል መጋቢት 28/2006 ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደርግ አስታውቋል፡፡የአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል የፓርቲውን ደብዳቤ ተቀብሏል በዛሬው እለት የፓርቲው ተወካዩች ለአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል ስለ ሰልፉ የሚገልጽ ደብዳቤ በማስገባት ተመልሰዋል፡፡ሰላማዊ ሰልፉ በተያዘለት ቀነ ገደብ የፓርቲው ጽ/ቤት ከሚገኝበት ቀበና በመነሳት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ፊት ለፊት እንደሚጠናቀቅ የአዲስ አበባ አንድነት ህዝብ ግኑኝነት አቶ ያሬድ አማረ አስታውቀዋል፡፡
- See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=6496#sthash.IZARPn7R.dpuf

No comments:

Post a Comment

wanted officials