Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, March 9, 2014

የሴቶች ነፃነት ቀን በሚከበርበት ወቅት የኢህአዲግ አምባገነን ስርዓት ተቃውሞ አሰምታችኋል በሚል ሴቶችን አሰረ / Females arrested on March 8 day in Ethiopia

በሴቶች ነፃነት ቀን በሚከበርበት ወቅት የኢህአዲግ አምባገነን ስርዓት ተቃውሞ አሰምታችኋል በሚል የሰማያዊ ሴቶችንና አብረዋቸው የነበሩትን ሁሉ አስሯል፡፡ እጅግ አስገራሚው ክስተት ደግሞ የኢህአዲግ ሴቶች ሊግ ፣ የሴቶች ፎረም(ኢህአዲግ የሚያዘው) እና አገዛዙ ያስተባበራቸው በርካታ ማህበራት በነፃነት ሩጫውን ያሻቸውን እያሉ ሲያጠናቅቁ ነፃነትን እንፈልጋለን ፣ ፍትህ ናፈቀን ፣ የህሊና እስረኞች ይፈቱ ፣ ኑሮ መረረ ፣ ሴቶችን በማስፈራራት አምስት ለአንድ መጠርነፍ ይቁም እና የመሳሰሉትን የተቃውሞ ድምፅ ያሰሙ የነበሩ ሰላማዊ ታጋዮች መታሰራቸው ነበር፡፡ በዚህም የኢህአዲግ ስርዓት በሴቶች ቀን የሴቶችን መብት እንደማያከብር በይፋ አረጋግጧል ፤ ሀሳባቸውን በነፃነት መግለፃቸው ወንጀል ሆኖ አፍኗቸውል፡፡
ከስር የምታዩት ምስሎች የኢህአዲግ ደህንነቶችና ፖሊሶች ሴቶችን እየለቀሙ ሲያፍሱና ሲይዙ ያሳያል
ድል ለኢትዮጵያ ሴቶች
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
የእስረኞች ስም ዝርዝር
1 ንግስት ወንድይፍራ(የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ)
2 ወይንሸት ሞላ (የምክርቤት አባል)
3 ወይኒ ንጉሴ(አባል)
4. እመቤት ግርማ(አባል)
5. ሜሮን አለማየሁ (አባል)
6. ምኞት መኮንን(አባል)
ለጊዜው የሴቶች ጉዳይ እና የህግ ጉዳይ ኮሚቴ የሆኑት ኢየሩስ ተስፋው እና ኤልሳ ወሰኔ ያሉበትን ልናውቅ አልቻልንም፡፡
ከነዚህ ሴቶች በተጨማሪም በቦታው የነበሩት የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አቶ ብርሀኑ ተ/ያሬድ ፤ የድርጅት ጉዳይ ሀላፊው አቶ ጌታነህ ባልቻ እና የህዝብ ግንኑነት ኮሚቴ አቶ አቤል ኤፍሬም ናቸው፡፡
እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ አቤል ኤፍሬም በአከባቢው ስለነበሩ ብቻ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ያሉበትን ለማጣራት የሰማያዊ ወጣት ክንፍ አባላት በእንቅስቃሴ ላይ መሆናችንን እያስታወቅን የደረስንበትን ይፋ የምናደርግ መሆኑን እናስታውቃለን፡
ትግሉን በእስራት እና በግድያ ማስቆም አይቻልም!!






Federal police scrambled to arrest female activists]
The notorious Ethiopian government federal police scrambled to arrest female activists, during protest broken out at women’s 5km run. Some of the arrested women are Negest Wondyfra, Woynshet Molla, Weyni Neguse, Emebet Girma, Meron Alemayehu and Mignot Mekonnen are some of the arrested Semayawi party members and supporters.


No comments:

Post a Comment

wanted officials