Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, March 6, 2014

በንፋስ ስልክ ላፍቶ የመንግስት ታጣቂው የባለ3 ልጆች ባለትዳሮችን በጥይት ደብድቦ ገደለ




ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው
በንፋስ ስልክ ላፍቶ የመንግስት ታጣቂው የ3 ልጆችን ባልና ሚስትን በጥይት ደብድቦ መግደሉ ተሰማ። ድርጊቱ የተፈፀመው ትላንት ከቀኑ 9.30 አካባቢ ነው ተብሏል።
አዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ውስጥ ልዩ ስሙ መካኒሳ አቦ ማዞሪያ በሚባል አካባቢ አንድ የመንግስት ታጣቂ የሶስት ልጆች ወላጆች የሆኑትን ባልና ሚስት በአውቶማቲክ መቺንገን በጥይት ደብድቦ ገድሏቸዋል።
የአካባቢው ሰዎች እና የሟች ዘመዶች በጋራ በመሆን የቀብሩን ስነ- ሥርዓት ለማስፈጸምና የመንግስት ታጣቂው የወሰደው እርምጃ ለማውገዝ እና በየጊዘው በአካባቢው የሚፈጸመውን የመንግስት ታጣቂዎች እርምጃ እና በህብረተሰቡ ላይ የደረሰውን ግፍ በጋራ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ለማጋለጥ በህብረት ድምጻቸውን ለማሰማት ሲሞክሩ በፈደራል ፖሊስ የተበተኑ ሲሆን በአካባቢው ላይ የአዲስ አበባ የፖሊስ ሃይሎች ተሰማርተዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials