Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, February 1, 2017

የሰማያዊ ፓርቲ እመራሮች ከ ድርድሩ ጋር በተያያዘ በ ፓርቲ ፅህፈት ቤት ተደበደቡ!

የሰማያዊ ፓርቲ እመራሮች ከ ድርድሩ ጋር በተያያዘ በ ፓርቲ ፅህፈት ቤት ተደበደቡ!
የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋና የድርጅት ጉዳይ ሀላፊው ኢ/ር ስሜነህ ፀሀይ በሆስፒታል ይገኛሉ።
ወያኔን ጭንቅ ውስጥ የከተተው የዲፕሎማቶችና የአለምአቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ጫና ወያኔ እንደራደር የሚል አጀንዳ ይዞ እንዲቀርብ አስገድዶታል።
የወያኔን የድርድር ባህል ላለፉት 25 አመታት እነሱ እንደሚሉት ሰጥቶ መቀበል ሳይሆን ስምምነት ኖረም አልኖረም የተነገረውን ሰምቶ አሜን ብሎ ተቀብሎ መሄድ ብቻ ነበር ነገር ግን ሰማያዊ ፓርቲ መኢአድንና መድረክን አስተባብሮ ይዞት የመጣው ከድርድር በፊት ቅድመ ሁኔታ አለን የሚለው ሀሳብ በወያኔ አደራዳሪውዎች የተወደደ አይመስልም ።
ከታጠቁ ደህንነቶች ጋር አብረው ፅህፈት ቤቱን ከወረሩት ደህነቶች ጋር የቀድሞ የፓርቲው የፓርቲው ም/ሊቀመንበር አቶ ስለሺ ፈይሳ ይገኙበታል በመባሉ አስተያየት የጠየቅናቸው አቶ ስለሺ እነዚህ ሰዎች መደብደብ ሲያንሳቸው ነው ብለውናል
Please click the following link to listen his opinion
ቀጣይ የድርድሩ ሂደት ምን ሊመስል እንደሚችል አልታወቀም።
የፓርቲውን ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ እንደሻውንና የፓርቲውን ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋን አነጋግረናቸዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials