Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, February 23, 2017

ታዋቂው የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ክለብ አጥቂ ድዋይት ዮርክ በፕሬዝዳንት ትራምፕ ፓሊሲ ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ታገደ


ታዋቂው የቀድሞው የማንችስተር ዩናይትድ እግር ኳስ ክለብአጥቂ ድዋይት ዮርክ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አጨቃጫቂውየኢምግሬሽን ፓሊሲ ሌላኛው ሰለባ መሆኑ ታወቀ ።


ከኳታር ወደ ሪፐብሊክ ኦፍ ትሪኒዳድ (Republic of Trinidad and Tobago) ለመብረር ማያሚ ላይ ግዴታትራንዚት ማድረግ ይገባው የነበረው የቀድሞው የማንችስተርዩናይትድ ኮከብ ድዋይት ዮርክ ወደ ማያሚ የሚበር አውሮፕላን ውስጥ እንዳይገባ መከልከሉ ታውቋል ።


ባሳለፍነው አርብ በፍሎሪዳ ሁለት የኢምግሬሽን ባለስልጣናት ድዋይት ዮርክ ወደ ማያሚ እንዳይገባ እንዳገዱት መረዳት ተችሏል ።


ከሁለት አመት በፊት በ2015እኤአ ድዋይት ዮርክ በኢራን ዋና ከተማ በሆነችው ቴራን ለስታዲየም ማስመረቂያ በተዘጋጀ የገቢ ማሰባሰቢያ የእግር ካስ ጨዋታ ላይ ተሰልፎ በመጫወቱ ምክንያት ወደ ማያሚ በሚያቀናው አውሮፕላን እንዳይሳፈር መደረጉተዘግቧል ።


የቀድሞው የማንችስተር ዩናይትድ አጥቂ ድዋይት ዮርክ ይህን በቴራን በ2015እኤአ የተካሄደውን የገቢ ማሰባሰቢያ ጨዋታካደረገ በሃላ እንኳን ኢራን አለማደሩን አሳውቋል ።


ይሁን እንጂ በአጨቃጫቂው የፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢምግሬሽን ፓሊሲ መሰረት ማያሚን ለትራንዚት መርገጥ እንደማይችልእንደተነገረው ድዋይት ዮርክ ገልጻል ።


“እየተከሰተ ያለውን ነገር ለማመን እጅግ ነበር የከበደኝ ። በቁጥር መግለጸ ከምችለው በላይ ወደ አሜሪካ ከዚህ በፊትተመላልሻለው። አገሪቷን እወዳታለው ። አሁን ግን እንደ ወንጀለኛ ነው የተቆጠርኩት።” በማለት ዮርክ በፍሎሪዳ ስለገጠመውእገዳ አስተያየቱን ሰጥቷል ።


ወደ ማያሚ በሚበረው አውሮፕላን ውስጥ ከገባ ወደ ኳታር በሃይል እንዲመለስ (deport) እንደሚደረግ ሁለት የኢምግሬሽንባለስልጣናት አስጥንቅቀው እንዳስገዱት ዮርክ በተጨማሪ ተናግሯል ።


ድዋይት ዮርክ ለሁለቱ የኢምግሬሽን ሰራተኞች በኳታር እንደማይኖር ለማስረዳት ቢሞክርም ባለስልጣናቱ ውሳኔያቸውን ለመቀየርእንዳልቻሉ ገልጻል ።

አባይ ሚዲያ ዜና በዘርይሁን ሹመቴ 

No comments:

Post a Comment

wanted officials