Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, April 10, 2014

የሚሊዮኖች ድምጽ – ሲያትሎች ከደብረ ታቦር ጎን በመቆም የሚሊዮኖች አንዱ ሆኑ !


የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ አራት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በደሴ ሰላማዊ በማድረግ የተጀመረ ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች በማድረግ ይቀጥላል።
በደሴ ከተማ የተደረገዉን እንቅስቃሴ በደንቬር የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ስፖንሰር ያደረጉት ሲሆን፣ በአዲስ አበባ የሚደረገዉን የመጀመሪያው እንቅስቅሴን ላስ ቬጋሶች፣ ሃዋሳ አትላንታዎች፣ ድሬደዋን የደብተራ ፓልቶክ ክፍል፣ ቂጫን ደግሞ የቃሌ ፓልቶክ ክፍል፣ ስፖንሰር እንደሚያደርጉ መግለጻችን ይታወቃል።
ሲያትል ዋሺንግተን ከደብረ ታቦር (ደቡብ ጎንደር ዞን) ከተማ ጋር ሶሊዳሪቲ በመመሰረት ፣ በደብረ ታቦር የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን በሚሊዮኖች ድምጽ ዘመቻ በከተማቸው ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሚያስፈልገውን ወጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን የተዘጋጁ ሲሆን፣ ሲያትሎች እኛም «ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» እያሉ ነው።
ይህ የሚሊየነሞች እንቅስቃሴ የአንድ ፓርቲ እንቅሳቅሴ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንደመሆኑ፣ በአገራችን ዴሞክራሲና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ሊቀላቀሉት፣ ሊደግፉት፣ የራሳቸው ሊያደርጉት የሚገባ እንቅስቃሴ ነዉ። ይህ እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች እንቅስቃሴ ነው። የእያንዳንዳችን እንቅስቃሴ ነው። ነጻነት ርካሽ አይደለም። ዋጋ ያስከፍላም።

No comments:

Post a Comment

wanted officials