Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, December 19, 2014

በአዲስ አበባ በኑር (በኒ) መስጅድ ህዝበ ሙስሊሙ ድንገተኛ ተቃውሞ አደረገ

bbn
(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ በኑር (በኒ) መስጅድ ህዝበ ሙስሊሙ ድንገተኛ ተቃውሞ በማድረግ አስገራሚ ተቃውሞውን ገለጸ::
ድንገት በተደረገው በዚህ ተቃውሞ ላይ የተለያዩ መፈክሮችን የያዙ ፊኛዎች ወደ ተውለብለበዋል ያሉት ዘገባዎች ፊኛዎቹ የተለያዩ መፈክሮች የተጻፈባቸው ሲሆን ከነዚህም መካከል : -” ትግሉ ይቀጥላል ፍትህ ነጥፏል ፤ሂጃብ መለያችን፤ኒቃብ ውበታችን ፤ትግላችን ቀጥሏል ፍትህን ማዘግየት ፍትህን መንፈግ ነው ፤ትግላችን እንደቀጠለ ነው” የሚሉ እንደሚገኙበት ዘግበዋል;;
በተጨማሪም “ፍትህ ፍትህ ፍትህ ;We Need Justice ፤Hijab Is Beauty ፤ justice Is Denied የሚሉት መፈክሮች ይገኙበታል፡፡” ያሉት ዘገባዎቹ በርካታ ፊኛዎች የተውለበለቡና ወደ ሰማይ የተለቀቁ ሲሆን ተቃውሞው በከፍተኛ ድምቀት ተከናውኗል ሲሉ ገልጸዋል::
የዛሬው የበኑር መስጅድ ተቃውሚ መንግስት በሴኩላሪዝም ሽፋን እየፈጸመ ያለውን የሂጃብ ገፈፋ የሚያወግዝ ሲሆን በተጨማሪም በህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ እጸፈጸመ ያለውን የፍትህ መዛባት ፤ በማረሚያ ቤቱ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማውገዝ ነው የሚሉት አስተባባሪዎቹ መንግስት ሙሉ በሙሉ ተቋሞውን በሃይል አስቁሚያለሁ ሲል የነበረ ሲሆን ህዝበ ሙስሊሙ ግን ድንገተኛ ተቃውሞ በማድረግ አስገራሚ ተቃውሞውን ገልጹዋል፡፡
ስለዛሬው ስልፍ ቢቢኤን በሰበር ዜናው ያስደመጠውን ያድምጡ

No comments:

Post a Comment

wanted officials