Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, May 6, 2016

ሰበር ዜና —4 የህወሃት ብሄራዊ መረጃ ከፍተኛ ሚስጥራዊ አባላት ተገደሉ



የብሔራዊ መረጃ የቅድመ ዝግጅት ማሰራጫና ማከናወኛን ክፍል መሰረት ባደረገ መልኩ ለመረጃ ክፍሉ ሐገር ለሐገር እየተዟዟሩ ሲሰልሉና ወሬ ሲያቀብሉ እንዲሁም ያለአግባብ ወገኖቻችንን ሲያሳስሩና ሲያስገድሉ የነበሩ አራት ቁልፍ የህወሃት ደህንነት አባላቶች መገደላቸዉን ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል። ተጠሪነታቸዉ ለመረጃዉ ክፍል ዳይሬክተር ብቻ እና በከፍተኛ ሚስጥር ከሌሎች አባላት እንኳ በተሰወረ መልኩ የሚንቀሳቀሱ ብዛት ያላቸዉ አባላቶች ላይ እርምጃዎቹ ያነጣጠሩ ናቸዉ ሲሉም ምንጮቻችን የገለጹ ሲሆን እርምጃ የተወሰደባቸዉ ግለሰቦችን ስም ዝርዝር ከዚህ በታች አስቀምጠዋል ።

1. አቶ በኩር ባዘዘዉ ገብረህይወት
2. ቀሲስ ትንሳኤ ሃይለ መለኮት
3. ሲስተር ሳምራዊት በቃሉ
4. መምህር ጣፋ አጋፋሪ

በየካቲት 28/2008 ለመረጃዉ ክፍል የወረደዉ የሞት መርዶ ብዙዎችን ያስደነገጠ ከመሆኑን ባሻገር የአራቱም ግለሰቦች አሟሟት በተመሳሳይ ወቅትና በተለያየ ክልል መሆኑ እንዲሁም አራቱም ከተገደሉ በኋላ ለመረጃ ክፍሉ ካልታወቁ ግለሰቦች የስልክ ጥሪ ተደርጎ በሐገሪቷ ላይ እየተካሄደ ያለዉ አፈናና ግድያ እስካልቆመ ድረስ እርምጃዉ እንደሚቀጥል ማስጠንቀቂያ መሰጠቱ ዉጥረቱን አባብሶታል።

በተለይም በኦሮሚያ ክልል እና በጎንደር እንዲሁም በኦጋዴን ክልል አካባቢ ተሰማርተዉ የነበሩ የመረጃዉ ክፍል ሰራተኞች በሙሉ እርምጃ ሊወሰድባቸዉ እንደሚችል የጠቆሙት ምንጮቻችን በእነዚህ ክልል የተሰማሩ አባላቶች ጠርገዉ እየወጡ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል ብለዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

No comments:

Post a Comment

wanted officials