Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, October 17, 2015

በትግራይ ሽሬ አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 4 ልጆችን በሰላም ተገላገለች








(ዘ-ሐበሻ) በትግራይ ክልል በሽሬ እንደስላሴ ቀበሌ 05 ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ ኢልሃም ብርሃኑ በሽር በአንድ ጊዜ የአራት ልጆች እናት ሆነች::

የአራት ልጆች እናት የሆነችው ወ/ሮ ኢልሃም በሽር ከባለቤቷ ከማል አብዱልዋስ ጋር የጋብቻ ስነስርዓቷን የፈጸመችው ሰኔ 3 ቀን 2005ዓ.ም ነበር፡፡ ይህች ወጣት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆችን የተገላገለችው እዚያው ሽሬ እንደስላሴ ውስጥ በሚገኘው ሱኁል ሆስፒታል መሆኑንም ታውቋል::

ለዘ-ሐበሻ እንደደረሰው መረጃ እናት ወ/ሮ ኢልሃም አራት ልጆችን በአንድ ጊዜ ከተገላገለች በኋላ “በ እርግዝና ወቅት ምንም የተለየ የሚሰማኝ ስሜት አልነበረም; በጥሩ ሁኔታ በሰላም ተገላግያለሁ” ብላለች:: አራቱን ልጆች ያዋለዱት ዶ/ር እዮብ ገላን “ወ/ሮ ኢልሃምም ሆነ ልጆቿ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ” ብለዋል::



No comments:

Post a Comment

wanted officials