Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, October 22, 2015

ድፍን የአዲስ አበባን ህዝብን ያስለቀሰ የመኪና አደጋ – ልትወልድ ቀናት የቀሯት ወጣት ሕይወቷ ተቀጠፈ






በኢትዮጵያ እየወጡ መቅረት የተለመደ ሆኗል – በተለይ በመኪና አደጋ:: ከ ዕለት ወደ እለት በሃገሪቱ በሚደርሰው የመኪና አደጋዎች በርካቶች ሕይወታቸው እያለፈ ነው::

ከላይ በፎቶ ግራፍ የምትመለከቷቸው ሁለት ጥንዶች ዳንኤልና የወብዳር ይባላሉ።ከ8 ወር በፊት እጅግ ደማቅ በሆነ ሁኔታ የሰርግ ስነስርአታቸውን አክብረዋል።
ዮብዳር በአንድ የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኛ ነች ። በማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማታው የትምህርት ዘርፍ በመከታተል ላይ ነበረች ።
ወጣቷ ልጅ ወልዶ የመሳም ጽኑ ምኛት ነበራት ይህንንም ለማሳካት ጥቂት ቀናት ነበር የቀራት ሆንም ግን በትናንትናው እለት ቀትር ላይ ኦሎምፒያ ሸዋ ዳቦ አካባቢ በደረሰባት አሳቃቂ የመኪና አደጋ ህይወቷ አልፏል ።
የቀብር ስነስርአቷም በዛሬው እለት በቀጨኔ መድሀኒያለም ቤተክስቲያን 9 ሰአት ላይ ይፈጸማል።

በኢትዮጵያ እየደረሰ ያለው የመኪና አደጋ እጅግ አሰቃቂ ነው:: ሰው አምኖ ለመንዳትም ሆነ ለመሳፈር እየተቸገረ ያለበት ሁኔታ ብቻ ሳይሆን በመንገድ ላይ መሄድ የሚያስፈራበት ደረጃ ላይ ተደረሷል:: በቀጣይ የምትመለከቱት ፎቶ ግራፍ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት የመጀመረው ባቡር መንገድ ላይ የገባውን አውቶቡስ ነው::



Abraham

No comments:

Post a Comment

wanted officials