Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, October 19, 2015

የአብዱ ኪያር “አልተለያየንም” ዘፈን በመንግስት ሚድያዎች እንዳይተላለፍ ታገደ

(ዘ-ሐበሻ)
 ድምፃዊ አብዱ ኪያር “አልተለያየንም” በሚል በአዲሱ የ”ጥቁር አንበሳ” ሲዲው ላይ ያቀረበው ዘፈን በመንግስታዊ ሚዲያዎች ላይ እንዳይተላለፍ ዕግድ መተላለፉን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከአዲስ አበባ አስታወቁ:: “በካርታ ብንለያየም – ኢትዮጵያም ኤርትራም አንድ ናቸው”… “አዲሱ ማንነቴን መቀበል አቃተኝ”… “በወላይታ ሙዚቃ ይጨፈራል በአስመራ”… የሚሉ መል ዕክቶች ያሉት በአንድነት ዙሪያ የሚያጠነጥነው ይኸው የአብዱ ኪያር ዘፈን በኢትዮጵያ ሁሉም ከተሞች ባሉ ሙዚቃ ቤቶች; በምሽት ክለቦችና መዝናኛ ቦታዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመጠ እንደሚገኝ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል:: መንግስታዊ ሚድያዎች እንዳያሰሙት የተከለከለው ይኸው “አልተለያየንም” የሚለውን ዘፈኑን ዘ-ሐበሻ እዚህ ጋብዛችኋለች:: ያድምጡት:: ለወዳጅ ዘመድዎም ያካፍሉት::


የአብዱ ኪያር “አልተለያየንም” ዘፈን በመንግስት ሚድያዎች እንዳይተላለፍ ታገደ

No comments:

Post a Comment

wanted officials