ሰሎሞን አባተ – ኒው ዮርክ
የጅቡቲ ፐሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ኤርትራን ባልተገባ ባሕርይና በነገረኛነት ከስሰዋል፡፡ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰባኛ ጠቅላላ ጉባዔ ባደረጉት ንግግር ፕሬዚዳንቱ ይህንን ክሣቸውን ያሰሙት ፕሬዚዳንት ጌሌ “ኤርትራ ለአካባቢውና በአጠቃላይም ለዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ አደጋ ነች” ብለዋል፡፡
የጅቡቲ ፐሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ኤርትራን ባልተገባ ባሕርይና በነገረኛነት ከስሰዋል፡፡ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰባኛ ጠቅላላ ጉባዔ ባደረጉት ንግግር ፕሬዚዳንቱ ይህንን ክሣቸውን ያሰሙት ፕሬዚዳንት ጌሌ “ኤርትራ ለአካባቢውና በአጠቃላይም ለዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ አደጋ ነች” ብለዋል፡፡
በአውሮፓ አቆጣጠር ከ2008 ዓ.ም አንስቶ የኤርትራ ወታደሮች የሰሜናዊ ግዛቶቻቸውን አንዳንድ አካባቢዎች ያለአግባብ ከተቆጣጠሩ በኋላ በዚህም ዓመት ውጥረትና ውዝግቡ መቀጠሉን የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ተናግረዋል፡፡ የመንግሥታቸው ባለሥልጣናትና እራሳቸውም በተደጋጌሚ ጉዳዩን ለማስረዳት ወደ ኒው ዮርክ መመላለሳቸውን አመልክተዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰባኛ ጠቅላላ ጉባዔ ያደረጉትን ንግግር ለመስማት ከዚህ ሥር ያለውን ማገናኛ ተጭነው ይከተሉ፡፡
Source -VOA
No comments:
Post a Comment