Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, October 29, 2015

ፖሊስ መምህር ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ስር አዋለ

ዘገባው የፋና ብሮድካስቲንግ ነው።

ፖሊስ መምህር ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ስር አዋለ
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 17 ፣ 2008 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ መምህር ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ስር አዋለ።
የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ምንጮች መምህር ግርማ ዛሬ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ተናግረዋል።
መምህር ግርማ በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት በማስተማርና በማጥመቅ ሲያገለግሉ የነበሩ ናቸው።
ይሁን እንጂ መምህሩ በማጥመቅ እና በማስተማር በሃገር ውስጥም ይሁን በውጭ ሃገራት ቤተክርስቲያኒቱን ወክለው እንዳያገለግሉ እውቅና መነፈጋቸውን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነገጋረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጠቅላይ ቤተክህነት አረጋግጧል።
የፋና ምንጮች መምህር ግርማ ከአገልግሎታቸው ጋር በተያያዘ በወንጀል ሳይጠረጠሩ እንዳልቀረ ነው የተናገሩት።
ጣቢያችን ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን እየተከታተለ ያቀርባል።
በጥላሁን ካሳ እና ብርሃኑ ወልደሰማያት
ምንጭ: http://www.fanabc.com/index.php/news/item/11255-ፖሊስ-መምህር-ግርማ-ወንድሙን-በቁጥጥር-ስር-አዋለ.html

No comments:

Post a Comment

wanted officials