Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, October 20, 2015

አራቱ የዞን ዘጠኝ አባላት ከተከሰሱበት ወንጀል ነፃ ተባሉ


• በፍቃዱ ሀይሉ በወንጀለኛ ህጉ እንዲከላከል ተብሏል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሰው አንድ አመት ከአምስት ወር በላይ ፍርድ ቤት ሲመላለሱ የቆዩት የዞን ዘጠኝ አባላት ከተከሰሱበት የሽብር ወንጀል መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ተወስኗል፡፡ የልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 5/2008 በዋለው ችሎት ከዞን ዘጠኝ አባላት መካከል 1ኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ፣ 3ኛ ተከሳሽ ናትናኤል ፈለቀ፣ 5ኛ ተከሳሽ አጥናፍ ብርሃኔና 7ኛ ተከሳሽ አቤል ዋበላን መከላከል ሳያስፈልጋቸው ተከሰውበት ከነበረው የሽብር ወንጀል ነፃ በመሆናቸው ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል፡፡
በሌላ በኩል 2ኛ ተከሳሽ በፍቃዱ ሀይሉ በብሎግ ወጥተው በማስረጃነት ከቀረቡበት የፅሁፍ ማስረጃዎች መካከል አመፅ ቀስቃሽ ናቸው በተባሉት ፅሁፎች ከሽብርተኛ ወንጀል ወጥቶ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 557/ሀ እንዲከላከል ተወስኗል፡፡ በፍቃዱ ሀይሉ በዋስ እንዲወጣ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን የዋስትናውን ጉዳይ ለማየት ለጥቅምት 10/2008 ዓ.ም ተቀጥረሯል፡፡
የዞን ዘጠኝ አባላት ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ ለአንድ አመት ከአምስት ወር ያህል ብይን ሲጠባበቁ የቆዩ ሲሆን ለብይን 5 ጊዜ እንዲሁም በአጠቃላይ ለ38 ጊዜ ፍርድ ቤት ተመላልሰዋል፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials