Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, September 9, 2016

በቺካጎ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሕወሓት መንግስት የተገደሉ ወገኖቻቸውን በጸሎትና ሻማ ማብራት አሰቡ


በቺካጎ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሕወሓት መንግስት የተገደሉ ወገኖቻቸውን በጸሎትና ሻማ ማብራት አሰቡ






(ዘ-ሐበሻ) በኢሊኒዮስ ግዛት ቺካጎ ከተማ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሃገር ቤት በትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት የተገደሉ ወገኖቻቸውን በአንድ ላይ ተሰባስበው በጸሎት እና በሻማ ማብራት ማሰባቸውን የዘ-ሐበሻ የቺካጎ ወኪል ጋዜጠኛ ዘላለም ገብሬ ዘገበ::

ዛሬ በቺካጎ ከተማ ፎስተር ቢች የተሰባሰቡት ኢትዮጵያውያን ለወገኖቻቸው የሻማ ማብራት እና የጸሎት ፕሮግራም ካደረጉ በኋላ እጃቸውን ወደ ላይ በማጣመር በሃገር ቤት እየተደረገ ያለው ትግል አጋርነታቸውን አሳይተዋል::

በሕወሓት መንግስት የተጎዱ ወገኖችን ለመርዳት ቃል የገቡት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን ለትግሉ የሚያስፈልገውን ነገር ለማድረግም ያላቸውን ቁርጠኝነት አሳይተዋል:: አዲሱን ዓመት በደስታ ሳይሆን ጥቁር በጥቁር በመልበስ በሃዘን እንደሚያሳልፉም አስታውቀዋል::



No comments:

Post a Comment

wanted officials