Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, April 30, 2015

(ሰበር ዜና) ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ በሊቢያ ኢትዮጵያውያን ሞተው የኔ 25ኛ ዓመት የሢመት በዓል እንዲከበር አልፈልግም አሉ

ዘ-ሐበሻ (ሰበር ዜና) ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ በሊቢያ ኢትዮጵያውያን ሞተው የኔ 25ኛ ዓመት የሢመት በዓል እንዲከበር አልፈልግም አሉ * በስደት ያለው ሲኖዶስ በሊቢያ ያለቁት ወገኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” ተብለው እንዲታሰቡ ወሰነ

holy sinod ethiopia

(ዘ-ሐበሻ) በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕጋዊ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ የ25ኛ ዓመት የሢመት በዓል ሰሞኑን እንደሚከበር ተገልጾ የነበረ ቢሆንም ፓትሪያርኩ “ወገኖቼ በሊቢያ በደቡብ አፍሪካ እና በአረብ ሃገራት እያለቁ የኔ በዓል እንዲከበር አልፈልግም” አሉ:: የበዓሉ መርሃ ግብር ተቀይሮም መታሰቢያነቱ በሊቢያ ለሞቱት መታሰቢያ እንዲሆን ጠይቀዋል::
ሲኖዶሱ ዓመታዊ ጉባኤውን በባልቲሞር መካነ ሰላም ኢየሱስ ቤ/ክ ዛሬ ያካሄደ ሲሆን በሊቢያ በአይሲኤል የተገደሉት 28 ኢትዮጵያውያን ልክ ሰማዕታተ ናግራን ተብሎ እንደሚዘከሩት “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” ተብለው እንዲዘከሩ መወሰኑን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል::
ፓትሪያሪክ አባ መርቆርዮስ በዓሉ አይገባኝም ያሉበትን ደብዳቤ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ:: ሲኖዶሱ በቀጣይ ቀናት ሰፊ መግለጫ ይሰጣል::
HH letter

No comments:

Post a Comment

wanted officials