Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, April 21, 2015

ሰልፋችን አሜሪካ ኤምባሲ ፥ቤተክህነት ና ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ቢያተኩር

የሞቱትን ነፍስ ይማር
ሁላችንም ቤተሰባቸው ስለሆንን ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን ይስጠን

ሁሌም እኛ ከሚገድሉ ሰዎች ጥብቅና የሚቆመው ወያኔ ኢትዮጵያዊ ስላልሆነ ሃገራችንን ለቆ እንዲወጣ ልቦና ይስጠው።
ባለፈው አመት በሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን በ አደባባይ ሲገደሉ በተቻለን መጠን የ ሳውዲ ኤምባሲ ጎን ቁጣችንን በሰላማዊ ሰልፍ ስንገልጽ ጻውዲ አረቢያን አትንኩብኝ ያለው ወያኔ ህወሃት አረባዊ እንጂ ኢትዮጵያዊነት የለዉም

በዚህ በሚያዚያ ወር ዓም በደቡብ አፍሪካ ዙሉ  ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች አፍሪካውያን  በህይወታቸው ሲቃጠሉ ከ ስምንት በላይ ሲሞቱ በርካቶች ሲቆስሉ የደቡብ አፍሪካ መንግስት ሆነ ሌሎች በጣም ያወገዙትን የኢትዮጵያ ገዢ ግን ጊዜያዊ ግጭት ነው ብሎ ያቀለለው የሰው ደም ለወያኔ ምንም ደንታ ስለሌለው አይደለም እንዴ?

ይሔው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ በደቡብ አፍሪካው ፍጅት አዝነን ሳንጨርስ ሚያዚያ በሊቢያ የመሸገው አይሲስ ሃያ ስምንት ኢትዮጵያውያንን እንደሽንኩት ከተፈ ገደለ። እነዚህም ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን አይሲስ፥ ቢቢሲ፥ ሲ ኤን ኤን፥ ሲሲቲቪ ወዘተ ሳይቀሩ እየመሰከሩ ዘረኛወ ወያኔ ግን ኢትዮጵያዊ መሆናቸው ቅድሚያ አልተጣራም ብሎ ከመዘገቡ በተጨማሪ ሃዘንተኞች አደባባይ እንዳይወጡና ህዝባዊ ቁጣውን ለማጨናገፍ ሲውተረተር  እያየነው ነው። በእርግጥ ህወሃት ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን ሳይሆን ብሄራቸውን ለማወቅ ያነሳሳውን ስንመለከት ፋሺስታዊ ነቀርሳው  ናዚያዊ ዘረኝነቱ  ብሶበት እንደሆነ እንረዳለን።



በየመንም በሳውዲ አረቢያም በሳውዝ አፍሪካም በሌሎች ሀገራትም ኢትዮጵያውያን ላይ ለሚደርሰው በደል ተጠያቂው፤ለስደታችን መንስዒ አሳዳጁ የህወሃት ብቻ ነው። ይሄንንም ለማየት ወደመስቀል አደባባይ የተመመው ሃዘንተኛ ወገን እያወገዘ ያለው ከ አ ይሲስ ይበልጥ  መንግስትን ነው።መንገድ ቢዘጋብንም ወደ ቤተመንግስት ቁጣችን ገንፍሎ ያመራነው  ያስቀጣን መንግስት እዛ ስላለ ነው።
ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ህወሃት ባላፉት ሃያ አራት አመታት ያሰራጨው የዘረኝነት መርዝ እንዲነቀል፥ ኢኮኒሚውን ሀወሃት መራሽ በሆነው ኢፈርት ከመመራት አልፎ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እንዲያድግ፥ እኛን በዘረኝነት በመተብተብ እና  በማደህየት እነሱ ረጀም እድሜ  እንዲኖሩ የሚሸርቡት ሴራ ላንዴና ለመጨረሻ አብቅቶ ሁሉም የኔ የሚለው ህዝባዊ መንግስት እንዲቋቋም የሃዘናችንን ቁጣ ወደ ህዝባዊ ሰልፍ እና ህዝባዊ አብዮት በተደራጀ መልኩ መመራት አለበት።

በመሆኑም
በ አዲስ አበባ እና በተለያዩ የሃገሪቱ ከተሞች የሚደረጉ የሃዘን መግለጫ አደባባዮች ላይ ለዚህ ሁሉ እልቂት ተጠያቂው የ ኢትዮጵያ መንግስት እንደሆነ በተለይም የሚሰጠው የንቀት መግለጫ ያበሳጨን መሆኑን የሚያሳውቁ መፈክሮች እንያዝ።
 በክፍለ ሃገራት ሰልፋችን ትናንሽ ፖሊስ ጣቢያዎችን፥ መገናኛ ብዙሃንን፥ ወታደራዊ ካምፖችን መውረር ላይ ያተኩሩ። ፖሊስ የህዝብ አካል እንደሆነ ያሳስቡት።
 በ አዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፋችን ከ አምስት ያልበለጡ መደራጃ መድረሻ ቦታዎች ቢኖሩት
ወደ አሜሪካ ኤምባሲ የሚሄድ ቡድን አይሲስ አሜሪካ በምታደርገው እርምጃ ተበሳጭቶ እየጨፈጨፈን በመሆኑ አሜሪካ ራሷን እንድታይ ማድረግ ፥
በተለይም ለወያኔ መንግስት ድጋፍ ማድረጓን አሜሪካ ታቁም ማለት ያስፈልጋል።

የ ኢትዮጵያ ቤተክህነት የመንግስት ተገዢ መሆኑ እንዲቆም ሰልፋችን አምስት ኪሎ በሚገኘው መንበረ ፓትርያርክ ላይም መደረግ ኣለበት።

የሊቢያ ኤምባሲ የሚገኘው  ከኢቲቪ ጎን በመሆኑ  በላይ በኩልም ራዲዮ ፋናን ለመቆጣጠር ከመርካቶ ከተክለ ሃይማኖት የሚነሳው ቡድን ሳይታሰብ ዱብ ቢል ከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ያለ ተማሪ ይቀላቀላል።
 በከተማዋ የሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች ባብዛኛው ተገደው እንጂ ጩሀት ብናሰማ መገልበጣቸው ስለማይቀር ትኩረታችን ጣቢያዎችን መማረክ ላይ ቢሆን

No comments:

Post a Comment

wanted officials