Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, April 29, 2015

ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች እየለጠፉ መሆናቸው ተገለፀ

ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች እየለጠፉ መሆናቸው ተገለፀ
የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች በመለጠፍ ላይ መሆናቸውን ሰማያዊ ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ በፃፈው ደብዳቤ አሳወቀ፡፡ ፓርቲው ለምርጫ ቦርድ በፃፈው ደብዳቤ አዲስ አበባ ውስጥ በትምህርት ቤቶች፣ በቤተ ክርስቲያናት፣ በወታደራዊ ካምፖች እንዲሁም በሌሎች ፓርቲዎች ዕጩ ፖስተሮች ላይ ያለ ፓርቲው ዕውቅና የሰማያዊ ፓርቲ ፖስተር እየተለጠፈ እንደሚገኝና ይህም የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሚፈጽሙት ተግባር እንደሆነ ገልጾአል፡፡
ይህንንም ተከትሎ ምርጫ ቦርድ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በተከለከሉ ቦታዎች ፖስተር እየተለጠፈ ነው›› የሚል ቅሬት በማቅረቡ ምን አልባት አባላት ተሳስተው ለጥፈው ይሆናል ብለው ፖስተሮቹን እንዳነሱ የገለጸው የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ ወጣት እያስፔድ ተስፋዬ ፖስተሮቹን ካስነሱ በኋላ በድጋሜ እነዚህ ቦታዎች ላይ ያለ ሰማያዊ እውቅና ፖስተሮቹ ተለጥፈዋል ብሏል፡፡ ፖስተሮቹን ለሁለተኛ ጊዜ ለማንሳት የሄዱት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትም መታሰራቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ወጣት እያስፔድ አክሎም ‹‹ከሰማያዊ ፓርቲ እውቅና ውጭ ፖስተሮች እየተለጠፉ ያሉት ገና ሰማያዊ ፖስተር ባልለጠፈባቸው አካባቢዎች ነው፡፡ እኛ ስናነሳ ደግመው ይለጥፋሉ፡፡ ለማንሳት የሚሄዱ አባላትንም ያስራሉ፡፡ ይህን እኩይ ድርጊትም ገዥው ፓርቲ ነው የሚፍጽመው ብለን እናምናለን፡፡ ይህን እያደረገ ያለው ሰማያዊን ሆን ብሎ ለመክሰስ ነው፡፡ ይህንንም ለምርጫ ቦርድ አሳውቀናል፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡ ፓርቲውም ‹‹ይህን ድርጊት ፓርቲያችን እንደፈፀመው ተደርጎ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት በኩል የተሰጠው ማሳሰቢያ ፓርቲያችን አይመለከተውም›› ሲል በደብዳቤው አሳውቋል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials