Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, April 16, 2015

በአማራ ክልል ሊመደብ የነበረው የኮማንዶ ጦር እቅድ ተሰረዘ * አለመተማመኑ በርትቷል



(ምንሊክ ሳልሳዊ) – የመጭው ምርጫ ጋር በተያያዘ ስጋቱ እያየለበት የመጣው የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አምባገነን ቡድን በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር እና በጎጃም ክፍለሃገራት ሊመድበው የነበረው የኮማንዶ ጦር እቅድ በጦሩ ውስጥ ያለውን ጉምጉምታ እና አለመተማመን ስላሳሰበው መሰረዙን እና ጦሩ ወደ ካምፕ እንዲመለስ መደረጉን ለጄኔራል ሰአረ መኮንን ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::



(ፎቶ ከፋይል)


ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ በጦሩ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እና ሕዝቡ በጦሩ ላይ ጫና እንደፈጠረ እንዲሁም የከተማ ፖሊሶች የሕዝብ ወገንተኝነት ማሳየታቸው የፌዴራል ፖሊሶች ግምገማ የፈጠረው ችግር የደህንነቶች መክዳት የህዝቡ ለውጥ መሻት ተደማምሮ አለመተማመኖች በስርአቱ ውስጥ እየሰፋ እንዲሄድ አድርጎታል::በሰራዊቱ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እየሰፋ እና እርስ በእርስ በጥርጣሬ መተያየት እየነገሰ መምጣቱ ሰራዊቱን በሕዝቡ መሃል ብናሰፍረው መሳሪያውን በመንግስት ባለስልጣናት ላይ ሊያዞር ስለሚችል በካምፕ እንዲቆይ እና በታትኖ ከአጋዚ ጦር ጋር መቀላቀል እና በተለያዩ አከባቢዎች ላይ እንዲመደብ የሚል ሃሳብ ቀርቧል::



የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ በከፍተኛ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ እየዳከረ በጠበንጃ ሃይል ሕዝብን ፈጅቶ ስልጣኑን ለማስረዘም እየሰራ መሆኑን ይታወቃል::ሰሞኑን የደረሱ መረጃዎች አዲስ አበባ በአጋዚ ጦር እና በፌዴራል ፖሊሶች እየተሸበረች መሆኗን መግለጹ ይታወሳል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials