Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, June 28, 2016

በላፍቶ ልዩ ስሙ ቀርሳ ኮቱማ በሚባለዉ አካባቢ በፖሊስና በነዋሪዎች መካከል በተነሳዉ ግጭት 17 ፖሊሶች መሞታቸዉን ነዋሪዎቹ ገለጹ።



በላፍቶ ልዩ ስሙ ቀርሳ ኮቱማ በሚባለዉ አካባቢ በፖሊስና በነዋሪዎች መካከል በተነሳዉ ግጭት 17 ፖሊሶች መሞታቸዉን ነዋሪዎቹ ገለጹ።
በአዲስ አበባ አካባቢ በላፍቶ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ቀርሳ ኮቱማ በሚባለዉ አካባቢ በፖሊስና በነዋሪዎች መካከል በተነሳዉ ግጭት 17 ፖሊሶች መሞታቸዉን ነዋሪዎቹ ለቢቢኤን ገለጹ። በፖሊሶችና የቀበሌ አመራሮች በ አካባቢዉ ያሉትን ቤቶች ለማፍረስ የመብራት ቆጣሪዎችን ለመንቀል ሲሞክሩ በተነሳዉ ግጭት ነዋሪዎቹ የፖሊሶቹን መሳሪያ በመቀማት፣በዱላና በድንጋይ በተከፈተ ጥቃት ነዉ ፖሊሶቹ የሞቱት።
ግጭቱን ተከትሎ የጦር መሳሪያን የታጠቁ የፌዴራል ፖሊሶች ወደ አካባቢዉ በመግባት ነዋሪዉን እየደበደቡ በጭነት መኪና እያፈሱ ወዳልታወቀ ቦታ እየወሰዱ መሆኑን ቢቢኤን ለማወቅ ችሏል። ህጻናትና እናቶች ያለቤት አባወራ ሜዳ ላይ እንደተጣሉና ለአደጋ እንደተጋለጹ ነዋሪዎቹ ያስረዳሉ።ጿሚዎች ማፍጠሪያ ምግብና ቦታ እንደሌላቸዉ ገልጸዋል። እራሳቸዉን ከፌዴራል ፖሊስ ጥቃት ለማዳን የሚሸሹ የቤት አባወራዎች በየጫካዉ ዉስጥ መቀመጣቸዉን፣ ምንገዶች ሁሉ መዘጋታቸዉን ነዋሪዎቹ ለቢቢኤን ገልጸዋል።ከነዋሪዎቹ ለመረዳት እንደተቻለዉ ቢያንስ አንድ የቀበሌ አመራር ሞቷል።









No comments:

Post a Comment

wanted officials