Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, June 16, 2016

የዐማራ ሕዝብ የመኖር ሕልውናው አደጋ ላይ ነው

የዐማራ ሕዝብ የመኖር ሕልውናው አደጋ ላይ ነው

ሙሉቀን ተስፋው
በአሜሪካን አገር የሚኖር አንድ ወዳጄ ሰሞኑን ቤት ልገዛ ነው አለኝ፡፡ ይህን ነገር ስሰማ በአእምሮዬ የመጣው ‹‹እንዴት በሰው አገር ቤት ለመሥራትና ቋሚ ንብረት ለማፍራት ጨከነ?›› የሚል ነው፡፡ ብዙ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ይኖራሉ፡፡ ባላቸው የትህምርት ዝግጅትና ችሎታ ከማንኛውም የዓለማችን ዜጎች ጋር ተወዳድረው የፈለጉትን ሥራ ማከናወን ብሎም ገንዘብ አጠራቅመው ቋሚ ንብረት ማፍራት ይችላሉ፡፡
ነገር ግን በዚህ ዘመን ዐማሮች በአሜሪካ ወይም በሌላው የዓለማችን ክፍል ሀብትና ንብረት ለማፍራት የሚደፍሩትን ያክል በኢትዮጵያ ውስጥ መብት የላቸውም፡፡ ለነገ ብለው የሚያስቀምጡት ጥሪት ዛሬ ምሽት ሊወድም ይችላል፡፡ ከሰሜን እስከ ደቡብ፤ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በየትኛውም ቦታና አካባቢ ዐማራ ሀብትና ንብረት ማፍራት አይችልም፤ ቢያፈራም በድንገት ሊወድምበት ይችላል፡፡
በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በጉምዝ፣ በአፋር፣ በሐረሪ፣ በሶማሌ፣ በትግሬ፣ በድረደዋ ብሎም በአዲስ አበባ ዐማሮች በይፋና በስልት ቀያቸውን ይለቃሉ፤ ይገደላሉ፡፡ ለመሆኑ ስንቶቻችሁ በአዲስ አበባ የሚፈናቀለው ዐማራ ቁጥር ከጉራ ፈረዳና ከቤንሻንጉል ጉምዝ ከተፈናቀለው ዐማራ ድምር ውጤት በላይ እንደሆነ ታውቃላችሁ?
አዲስ አበባን መልሦ ማልማት በሚል ፈሊጥ ስንቶቹ የዐማራ ርስቶች እየተነቀሉ ለወያኔ ካድሬዎች ተሰጥተዋል? ልደታ የተፈናቀለው ዐማራ ስንት ነው? አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት የተነሱት ዐማሮች የት ሔዱ? ካዛንችስ ምን እየሆነ ነው? አሜሪካን ግቢ? ሽሮ ሜዳ? … አዲስ አበባ ላይ ያለው መልሦ ማልማት ሥራ ዐማሮችን ከመሃል ከተማ እያስወጡ ባተሌ ለማድረግ እንደሆነ ስንቶቻችን ተረዳን?
እንግዲህ ዐማሮች በቆረቆሩት ከተማ፣ በተወለዱበት ቀዬ፣ በአቀኑት አገር መብት የላቸውም፡፡ ለሚገድሏቸውና ለሚያፈናቅሏቸው አበል እንዲከፍሉ ይገደዳሉ፡፡ ዕውነት ለመናገር ስለ ዐማራ መናገር ‹ወገንተኛ› የመሆን እና ያለመሆን ጥያቄ አይደለም፤ የሰብአዊነት ጉዳይ ነው፡፡
((ከታች የሚታየው ምስል በመስከረም 2007 ዓ.ም. በጉራ ፈረዳ በገጀራና በድንጋይ የተገደለ ዐማራ ነው))

አማራን ነጥለው በጠላትነት የፈረጁት ፋሺስት ጣሊያን፣ ናዚ ጀርመን፣ ምእራባዊያን ኢምፔሪያሊስቶች፣ የወያኔ ትግሬና ሻቢያ
~~~~~~~~~~~~~~~~~
እነ መለስ ተክሌን የመሳሰሉ በቀድሞው የቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩ የትግሬና የኤርትራ ተወላጆች መሪነትና አነሳሽነት የተከፈተው ኢትዮጵያን በጎሳ የመከፋፈል ሴራና ጸረ አማራ ፕሮፓጋንዳ እንደ ዋለልኝ መኮንን ባሉ ጥራዝ ነጠቅ ቅጥረኞች ጽሁፍ አማካኝነት ገበያ ላይ ከመዋሉ እጅግ ቀደም ብሎ በጃን ሆይ ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖር በነበረ ባሮን ሮማን ፕሮቻዝካ የተሰኘ ናዚ ኦስትሪያዊ የአውሮፓ ዲፕሎማቶች ተወካይ ተጠንስሶ፣ “Abyssinia the Powder Barrel” በተሰኘ በ 1926 ዓ ም ባሳተመው መጽሃፉ የሰፈረና በነዋለልኝና ጌቶቹ ቃል በቃል የተቀዳ መሆኑን ከሚቀጥለው ንጽጽር መረዳት እንችላለን:: ይህ የባሮን ፕሮቻዝካ ጸረ ኢትዮጵያዊነትና ጸረ አማራነት ጽሁፍ ከጣሊያን ወረራ አንድ አመት ቀደም ብሎ ለህትመት የበቃ ሲሆን የአሜሪካንን እንግሊዘኛ ጨምሮ በ 15 የአውሮፓ ቋንቋዎች ተተርጉሞ በስፋት እንዲሰራጭ ተደርጓል::
ይህን መሰል ጸረ አማራ ፕሮፓጋንዳ በምእራባዊያን ዘንድ አማራ ለተሰኘ ነገድ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዲዳብር አስተዋጽኦ አድርጓል:: ጸጋዬ ገብረመድህን በአንድ ጦማሩ የአሜሪካ ሴኔት የአማራ ነገድ ጨቋኝና ጸረ ምእራባዊያን አመለካከት ያለው ነው ብሎ እንደሚያምን ኢትዮጵያዊያን በዋሽንግተን ዲሲ ባደረጉት ሰልፍ ላይ የሴኔቱ አባል የሆነ ግለሰብ የሰጠውን እጅግ ጸረ አማራ የሆነ መግለጫ ጠቅሶ አስነብቦናል:: ይህ ጸረ አማራ አመለካከት ይብዛም ይነስም አብዛኞቹ ምእራባዊያን ፖለቲከኞች የሚጋሩት እንደሆነ ከፖለቲካ ህይወት ልምዱ መታዘቡን ጸጋዬ ገብረመድህን በተጨማሪ ይገልጻል:: ጸጋዬ ለዚህ ምክንያት ሆኗል ያለውን ሲያስረዳ የወያኔ ትግሬዎችና እንደ ኦነግ ያሉ ጸረ አማራ ቡድኖች ለምእራባዊያን የመገቡት የተንሸዋረረና የጥላቻ የአማራ ነገድ ምስል ነው ይለናል:: ይህ ለኔ የዋህነት ነው:: ምእራባዊያን እንዲህ ጂኦ-ፖለቲካሊ እስትራቴጂክ ለሆነች ሃገር ፖለቲካ ባዕድ ሆነው አያውቁም:: ከአጼው ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ተከስተው ባለፉ አብዮቶችና አንኳር ፖለቲካዊ ክስተቶች፣ የርስበርስ ጦርነቶች፣ በኤርትራ የመገንጠል ጥያቄ፣ በስልሳዎቹ የተማሪዎች እንቅስቃሴ፣በታህሳሱ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራና በመሳሰሉት የምእራባዊያን በተለይም የዘመናችን ኢምፔሪያሊስት ሃገረ አሜሪካ ቀጥተኛና የእጅ አዙር ተሳትፎ እንደነበረበት በግልጽ የሚያሳዩ ብዙ የታሪክ መረጃዎች አሉ (የፕሮፌሶር አለሜ እሸቴን ስራዎች እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ)::
አሜሪካና አውሮፓዊያን ኢትዮጵያ እስከዛሬ ያለፈችባቸው የሃገሪቱን ገጽታና የምትመራበትን ርእዮተ አለም በአሉታዊ መልኩ ቀይረው ያለፉ ኩነቶችን ቅርጽ በማስያዝ የተጫወቱት ሚና ሃገር በቀሎቹ የኢትዮጲያዊነት ጠላቶች ሊኖራቸው ከሚችለው ሚና እጅግ የላቀ ነው:: የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲ አይ ኤ በተወካዩ ማይልስ ኮፕላንድ በኩል በግዜው “ሰልፊ ንጻነት” በመባል ይታወቅ የነበረውን የሻቢያን አመራሮች በሲ አይ ኤ አባልነት በመመልመልና የሻቢያን ተገንጣይ አላማና ግብ አሜሪካ በቀጠናው የነበራትን ኢምፔሪያሊስት አጀንዳ በሚጠቅም መልኩ በመቅረጽ እንዲሁም ሻቢያን በትጥቅና በሎጂስቲክስ በማጠናከር በኢትዮጵያ ህዝብና ሉአላዊነት ላይ የፈጸመው ክህደት ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው:: የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ክሊንተን ባለቤት የሆኑት ሚስስ ሂላሪ በኤርትራ “ንጻነት” ዋዜማ አስመራ ተገኝተው ጨቅላዋ ሃገራቸው አዛውንቷን ኢትዮጵያን ለማፍረስ ላበረከተችው አስተዋጽኦ በእቅፍ አበባና በሃገር ልብስ ስጦታ ተንቆጥቁጠዋል:: የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲ አይ ኤ በ 2000 ዓ ም እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ባወጣው አንድ ዶክዩመንት በኢትዮጵያ ያሉ ጎሳዎች የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት በዘመነ ወያኔ መጎናጸፋቸውን ገልጾ ስለ መጪው የኢትዮጵያ እጣፈንታ ሲተነብይ በዚህ የሃገሪቱ ፖለቲካዊ አብዮት ጥቅሙ የተነካበት አማራ የተባለው ጨቋኝ ነገድ የቀድሞ የበላይነቱን ለማስመለስ በሚያደርገው ጥረት ምክንያትነት ሃገሪቷ እንደምትፈራርስ ያትታል:: ነገሩን በጥልቀት ስንመለከተው በራሱ የሚተማመን፣ የሃገሩንና የህዝቡን ጥቅም የሚያስቀድምና ለነሱ ፍላጎት ታዛዥ ያልሆነ እምቢተኛ ስርዓት በየትኛውም ሃገር እንዳይፈጠርና እንዳያብብ በማንኛውም መንገድ ማረጋገጥ ተቀዳሚው ተግባራቸው ያደረጉት ምእራባዊያን ኢምፔሪያሊስቶች የአማራን ነገድ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት የቆመ የሃገሪቱ ጥቅም አስጠባቂ አድርገው የለዩት በመሆኑና የዚህ ነገድ በወሳኝ የሃገሪቱ የስልጣን እርከን ላይ መኖር በቀጠናው ላላቸው ኢምፔሪያሊስት አጀንዳ የማይመች መሆኑን በታሪክ ሂደት ስላመኑበት የአማራውን ነገድ ኢላማ ያደረጉ ተገንጣይ ሃይሎችን በጉያቸው ሸጉጠው ከመደገፍ በተጨማሪ በአማራው ላይ ለሚደርሱ ተደጋጋሚ ጉልህ ኢ-ሰብአዊ በደሎች ጆሮ ዳባ ልበስ ማለታቸውና ለወያኔ ትግሬ መንግስት እድሜ መርዘም ትልቁን ሚና መጫወታቸው የሚከተሉትን የጸረ አማራ ፖሊሲ ያስረግጥልናል :: እንደ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ሂውማን ራይትስ ዋች ያሉ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ሳይቀር የ 1993ቱ የወለጋው የአማራ ነገድ ጭፍጨፋና መፈናቀል ወቅት የአማራ ነገድን የቀድሞ “ጨቋኝነት” ገልጸው በጉዳዩ ጣልቃ ላለመግባት ያሳዩት ማመንታት የጸረ አማራ አመለካከቱ በምእራባዊያን ዘንድ ምን ያህል ስር እንደሰደደ ትልቅ አስረጅ ክስተት ነው::
የባሮን ፕሮቻዝካ መጽሃፍ ዛሬ የወያኔ ትግሬና ሌሎች ተገንጣይ ሃይሎች የየለት መዝሙር የሆነው የራስን እድል በራስ መወሰን የሚል የቃሉን ትርጉም የሚጣረዝ በታኝ አስተሳሰብ (“የእራስን” የሚለው ሃረግ ግለሰብን እንጂ የወል ስብስብን እንደማያመለክት ልብ ይለዋል) ለመጀመሪያ ግዜ በኢትዮጵያ ያስተዋወቀ ነው:: ይህ የፋሺስት የከፋፍለህ ግዛው ጽንሰ ሃሳብ ከፋሺስት ወረራ ማክተም በኋላ ለመጀመሪያ ግዜ በኢትዮጵያ ምድር ነፍስ የዘራው በስልሳዎቹ የተማሪዎች አመጽ ዘመን ኤርትራዊ የሚል የባርነት ማንነት በያዙ ተማሪዎች አማካኝነት ነው:: የኤርትራዊያንን ጥያቄ ለማለዘብና ለማቀፍ በሚል የስልሳዎቹ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የኢትዮጵያ ዋነኛ ችግር ነው ብሎ ያስቀመጠው ኤርትራዊያን ተገንጣዮች ይዘው የተነሱትን የራስን እድል በራስ መወሰን የሚለው ፋሺስታዊ ጽንሰ ሃሳብ እንደ መፍትሄ የሚቀርብበት “የብሄር ብሄረሰብ ጥያቄ”ን ነበር:: እንደ ታላቁ ምሁር ፕሮፌሶር መሳይ ከበደ እምነት ኤርትራዊያን ብሄርተኞችን ለማባበል ሲባል ተቀብለን በመላው ኢትዮጵያ ላይ የተገበርነው “የኢትዮጵያ ችግር የብሄር ጭቆና ነው” መፍትሄውም የራስን እድል በራስ የመወሰንን መብት ለመጎናጸፍ የሚደረግ ትግል ነው የሚለው የኤርትራ ብሄርተኞች በፋሺስት አመለካከት የተቃኘ አቋም ኤርትራን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያንም አሳጥቶናል:: ኤርትራ የሚል የባርነት ማንነት ከኢትዮጵያዊነት መንፈስ ጋር ፈጽሞ የተጣላ መሆኑን ያልተገነዘቡት ቀዳማዊ ሃይለስላሴና በዙሪያቸው የነበሩት እንደ አክሊሉ ሃብተወልድ ያሉ ፖለቲከኞች በአካል ድል የነሳነውን የቅኝ ገዢዎች መርዝ የቅኝ አገዛዝ ስሪታቸው በሆኑትና የኢትዮጵያዊነት የነጻነት መንፈስ ብል በሆኑት ኤርትራዊያን ተባዮች በኩል ጎትተው በማስገባት ሃገር አልባ ያደረገንን ታሪካዊ ቀይ ስህተት ባለማወቅና በየዋህነት ፈጽመዋል::
(የባሮን ፕሮቻስካ የጥላቻ መጽሃፍ ህትመትን ተከትሎ ባሮን ሮማን ፕሮቻዝካ በኢትዮጵያ መንግስት ከሃገር እንዲባረር መደረጉን ለአንባቢ ልንገልጽ እንወዳለን::)
የቀድሞው የኤርትራ አስገንጣይ ቡድን ጀብሃ ተላላኪ የነበረው ቅጥረኛው ዋለልኝ መኮንንና ኦስትሪያዊው የናዚ ፓርቲ አባልና የፋሽስት ሞሶሎኒ ደጋፊ የነበረው ባሮን ፕሮቻዝካ ኢትዮጵያዊነት ውሸትና የአማራው ፈጠራ ነው ሲሉ የሰበኩባቸው ጽሁፎች፥
ንጽጽሩን በዋለልኝ መኮንን የፋሺስት ፕሮፓጋንዳ ቅጂ ጽሁፍ እንጀምር:-
“የብሄር ትርጉም ከዚህ ውጪ ምንድን ነው? የራሱ የሆነ ቋንቋ፣ አለባበስ፣ ታሪክ እንዲሁም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አደረጃጀት ያለው ህዝብ ማለት አይደለምን? ይህ ከታወቀ ዘንዳ በኢትዮጵያ ውስጥ የኦሮሞ ብሄር፣ የትግሬ ብሄር፣ የአማራ ብሄር፣ የጉራጌ ብሄር፣ የሲዳማ ብሄር፣ የወላይታ ብሄር፣ የአደሬ ብሄር፣ እንዲሁም የቱንም ያህል ቢያስከፋችሁ የሶማሌ ብሄር መኖሩን ልገልጽ እወዳለሁ፡፡ ይህ ነው የኢትዮጵያ እውነተኛ ገጽታ፡፡ እርግጥ ነው ኢትዮጵያዊነት የተሰኘ በአማራው ገዥ መደብ አማካኝነት በሌሎች ብሄሮች ላይ ያለፍላጎታቸው በሃይል የተጫነ፣ በነዚህ ጭቁን አካላት ሳይቀር በየዋህነት የተገፋ የፈጠራና የውሸት ብሄራዊ ማንነት አለ:: ይህ ኢትዮጵያዊነት የተሰኘ የፈጠራ ብሄራዊ ማንነት ምንድን ነው? በቀላሉ የአማራው የበላይነት ማለት አይደለምን?”
( ዋለልኝ መኮንን ካሳ፤ “Struggle Magazine” ፤ ቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ፤ ህዳር 9፣ 1961 ዓ ም)
ለፋሺስት ጣሊያን የአምስት አመታት አገዛዝ እንደ መመሪያና “ማንዋል” ያገለገለው በጣሊያንኛ ትርጉሙ “አቢሲኒያ ፔሪኮሎ ኔሮ”(ABISSINIA PERICOLO NERO) ወይም “አቢሲኒያ ጥቁር አደጋ” የተሰኘው ኦሪጅናሉ የባሮን ፕሮቻዝካ ጸረ አማራና ጸረ ኢትዮጵያ መጽሃፍ ውስጥ ሰፍሮ የሚገኘው ሃሳብ እንደሚቀጥለው ይነበባል፥
“አንድ የሆነ አቢሲኒያዊ ህዝብ የሚባል ነገር የለም:: ክርስቲያን ያልሆኑት አብዛኞቹ የአቢሲኒያ ጎሳዎች ከአማራ ጭቆና እንደመላቀቅ የሚመኙት አንገብጋቢ ነገር የለም:: እነዚህ ከአናሳው የአማራ ጨቋኝ ጎሳ በቋንቋ፣ በባህልና በሃይማኖት የሚለዩት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ህዝቦችና ጎሳዎች የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት ቢሰጣቸው ኖሮ የአማራን የጭቆና ቀንበር ድሮ ገና አሽቀንጥረው በጣሉት ነበር:: ከዚህ ይልቅ ከአውሮፓዊያን ተጽእኖና ተራማጅ የአውሮፓ ቅኝ አገዛዝ ለሃገሪቱ ሊያመጣ ከሚችለው ጥቅሞች በአማራው ጎሳ አማካኝነት በሃይል እንዲነጠሉ ተደርገዋል:: ”
(“Abyssinia the Powder Barrel” by Baron Roman prochazka published in 1934.)
ፕሮ ቻዝካ ኢትዮጵያን በጎሳ ላይ ተመስርቶ ለመበታተን አውሮፓውያንን የጎተጎተበትን ምክንያት ከላይ በተጠቀሰው መጽሃፉ ውስጥ ሲያስረዳ እንደሚከተለው ይላል፥
“የዚህ ሃገር(የኢትዮጵያ) መንግስት በአለም አቀፍ ውሎችና ስምምነቶች ስር የተገቡ ግዴታዎች እንዳይሟሉ በረቀቀ ሴራ እያሰናከለ እንደሆነና ህዝቡም አለም በገሃድ በሚያውቀው የፈረንጅ ጥላቻቸውና በተጋነነ ብሄራዊ ንቃታቸው እየተገፉ የአለም ጥቁር ህዝቦችን በሙሉ ያቀፈና ያሳተፈ የጦር ግምባር በአብሲኒያዊያን አመራር ስር በማደራጀት በነጭ ዘር ላይ ሁሉ አቀፍ ጥቃት ለመሰንዘር አዲስ ኢትዮጵያዊ እንቅስቃሴ እያጧጧፉ እንደሆነ ለማሳየት እፈልጋለሁ:: የአቢሲኒያዊያን ጸረ ነጭ ፖሊሲ የመጨረሻ ግብ ከጃፓን ጋር ግንባር በመፍጠር የአፍሪካ ጥቁር ህዝቦች በሙሉ አዳኝ ሆኖ መውጣት ነው:: በአቢሲኒያ ውስጥ የሚገኙ የስልጡን ሃገራት ቆንጽላዎች አቢሲኒያዊያን የምእራባዊያንን ባህልና ስልጣኔ ጥቃት ከፍተው ከናካቴው ከማውደማቸው በፊት መንግስታታቸውን የማያወላውል ጠንካራ አቋም እንዲወስዱ የማስጠንቀቅ ግዴታ አለባቸው::”
(“Abyssinia the Powder Barrel” by Baron Roman prochazka published in 1934.)
የፋሺስት ፕሮፓጋንዲስት የነበሩት ፕሮፌሰር ራፋኤል ዲ ላውሮ በበኩላቸው ኢትዮጵያን በጎሳ ላይ ተመስርቶ በመከፋፈሉ ተግባርና በአማራው (በተለይም በሸዋ አማራ)የነጭ ጠላትነት ዙሪያ እንዲህ ብለው ይጽፋሉ:-
“በጎሳ ላይ ተመስርተው ለተቋቋሙት አምስት ክልሎች የመንግስት መቀመጫ ምርጫና የድንበር ማካለሉ ስራ የተከናወነው ፖለቲካዊ ጥቅሞችንና ተፈላጊ ውጤቶችን ሊያስገኙ የሚችሉ ግልጽ የሆኑ ፖለቲካዊ መመዘኛዎችን ተከትሎ ነው:: ህግ አውጪው አካል አንድ አይነት ቋንቋ፣ጎሳና የታሪክ ማንነት ያላቸውን የኢትዮጵያ ህዝቦች በአንድ መንግስት ስር የማጠቃለል መርሃችንን በሚገባ ተከትሎ ተግባራዊ አድርጓል:: የእነዚህ የኮሎኒያል ግዛቶቻችን ድንበር አከላለል በግልጽ እንደሚያሳየው የፋሺስት ህግ አውጪዎች በኢትዮጵያ ያለውን ፖለቲካዊ ሁኔታ፣ የሃገሪቱን ያለፉት አንድ መቶ አመታት ታሪክ የሚወክሉ የተለያዩ ኩነቶችንና ህዝቦችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በአትኩሮትና በጥንቃቄ ሰርተዋል:: የሸዋው መንግስት መገለጫ የሆነው በሌሎች የጫፍ ሃገር ህዝቦች ኪሳራ ሃገሪቱን የማማከል ዝንባሌ በሁሉም ዘንድ የታወቀ ነው:: ሸዋዎች ባጠቃላይ ለአውሮጳዊያን በተለይ ደግሞ ለጣሊያኖች ያላቸው ከፍተኛ ጥላቻ በደንብ የሚታወቅ ነው:: የቅኝ ግዛቶቻችንን ለማደራጀት ወይም ለማካለል የተጠቀምንበት መሰረታዊ ህግ (Legge Organica) በንጉሱ ዘመን የሁሉም ጸረ ጣሊያን እንቅስቃሴዎች ማእከል የነበረውን የሸዋን ግዛት ዛሬ ሸዋ የሚባል ግዛት በህልውና እንዳይኖር(ከካርታ ላይ እንዲነሳ)በተደረገበት ደረጃ ስሙን ጭምር በማጥፋት ይህን የሸዋ እባጭ(‘bubbone Scioano’) ማፍረጥ ችሏል::”
የወያኔ ትግሬ መንግስት ላለፉት 23 አመታት የአማራን ህዝብ ሰብአዊ ፍጡር ሳይሆን እንደ አንድ ሊጠፉ የሚገባው አደገኛ አውሬ አድርጎ ለመሳልና የተደራራቢ ቅጣት ሰለባ ለማድረግ የቻለበት መደላድል የተፈጠረው እንዲሁ ከምንም ተነስቶ አልነበረም:: የአማራው የገዛ ልጆች በቀንደኝነት የተሳተፉበት ለብዙ አስርተ አመታት ሲንከባለል የመጣና የተከማቸ የአማራን ማንነት የማጠልሸትና የማስነወር ተግባር ውጤት ነው:: የአማራውን ህዝብ ነጥሎ የማጥላላትና ማንነቱን የማጠልሸት ፕሮፓጋንዳ የተጀመረው እስከ ዛሬው እለት ድረስ “የኢትዮጵያዊነት ስሜት (የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ስሜት) የሌለውና የተከፋፈለ” በማለት መጥራትን በመረጡት የኢትዮጵያ ህዝብ የተባበረ ክንድ በአድዋ ጦርነት የደረሰባቸውን ከፍተኛ ውርደት ተከትሎ ከተሳሳተ አረዳድ በመነሳት ኢትዮጵያዊነትን ከአማራው ማንነትጋር ለማያያዝ በሞከሩ የጣሊያን ቅኝ ገዢዎች አማካኝነት ነበር:: ይህን በታላቁ ንጉስ አጼ ሚኒሊክ በሳል አመራርነት በኢትዮጵያ ህዝብ የተባበረ ክንድ የደረሰባቸውን አሳፋሪ ሽንፈት ተከትሎ ነው እንግዲህ ፋሺስት ጣሊያኖች አማራውን የጥቃት ኢላማ ማድረግ የጀመሩት:: የጣሊያናዊያን ኮሎኒያሊስት የስነጽሁፍ ውጤቶች አማራውን ጭራቅ አድርገው በሚስሉ ፕሮፓጋንዳዎች የታጨቁ ናቸው:: በዚህ አጋጣሚ እንደ ፔትሮ ባዶግሊዮ፣ አልቤርቶ ስባቺ፣ አንጄሎ ዴልቦካ፣ አንቶኒ ሞክለር ወዘተ ባሉ የጣሊያን ምሁራኖች አማራውን በተመለከተ የተጻፉ መጽሃፍትን ጉዳዩን በጥልቀት ለመረዳት ይረዳ ዘንድ ለአንባቢ እጠቁማለሁ:: የወያኔ ትግሬ መንግስት በ 5 አመቱ የፋሺስት ጣሊያን ወረራ ወቅት ጠላት በኢትዮጵያ ላይ ለመጫን የሞከረው የጎሳ ብሄርተኝነት አቀንቃኝ እንደመሆኑ መጠን ኢትዮጵያዊነትን(የኢትዮጵ
ያ ብሄርተኝነትን) በጠላትነት ፈርጆ ለማጥፋት በጽኑ ተንቀሳቅሷል:: በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ከተሳሳተ ስሌት በመነሳት የአማራውን ህዝብ የኢትዮጵያዊነት ብቸኛ ተቆርቋሪና አቀንቃኝ አድርገው በመነጠል እንደ ፋሺስቶች ሁሉ የጥቃት ኢላማ አድርገውታል:: ይህ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ብቸኛ አቀንቃኝ አማራው ነው የሚለው መሰረት የለሽ አተያይ ፋሺስት ጣሊያኖችን ብቻ ሳይሆን በ1997 ዓ.ም. ግንቦት ወር አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ በጎሳ ላይ የተመሰረተን ፖለቲካና የአናሳው የወያኔ ትግሬን የጎሳ አፓርታይድ ስርአት በመቃወም ባልጠበቁት መልኩ አደባባይ ወጥቶ በማየታቸው ከፍተኛ ድንጋጤን የፈጠረባቸው እንደ ወያኔና መድረክ ያሉ የጎሳ ብሄርተኛ ቡድኖችን ጭምር ያሳሳተ አረዳድ ነው:: አጼ ሚኒሊክ በታሪካችን ወደር በማይገኝለት የአመራር ብቃት የጣሊያን ፋሺስት ወራሪዎችንና የኤርትራ አሽከሮቻቸውን ጦር በአድዋ ጦርነት ድባቅ በመምታት አሳፍረው በመመለስ ኢትዮጵያን በአለም ጭቁን ህዝቦች የነጻነት ጮራነት የአለም ካርታ ላይ ለማስቀመጥ የመላው ኢትዮጵያ ህዝብን ታማኝነትና ትብብር መጎናጸፍና አንድ አድርገው ለአንድ ሃገራዊ አላማ ማንቀሳቀስ የመቻላቸውን እውነታ ለመካድ ወይም ላለመቀበል ጣሊያኖች በኮሎኒያሊስት ጽሁፎቻቸው ውስጥ ኢትዮጵያ የሚለውን ስም ላለመጠቀም በመወሰን በምትኩ አቢሲኒያ(አቢሲኒያ ማለት የዛሬው ሰሜናዊ ኢትዮጵያ ማለት ነው) የሚለውን ቃል በመጠቀም መቀጠልን መርጠዋል:: የፋሺስት ጣሊያን ከፋፋይ የጎሳ ርዕዮተ አለም አራማጅ የሆነው የወያኔ ትግሬ ቡድን እንደ ጣሊያኖች ሁሉ አማራውን የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ቀንደኛና አክራሪ አቀንቃኝ አድርጎ በመፈረጅ በነገዱ ላይ የኢኮኖሚያዊ ስነልቦናዊና አካላዊ ሁለንተናዊ ጦርነት በመክፈት ከምድረ ገጽ የማጥፋት እኩይ አላማውን እየገፋበት ይገኛል::
በዘመነ ኮሎኒያሊዝም ፋሺስት ጣሊያኖች የኤርትራዊያን ቅኝ ተገዦቻቸውን አእምሮ የዛሬው የኤርትራዊያን ማንነት ዋነኛ መገለጫ በሆነው የአማራ ጥላቻ መመረዝ ችለዋል:: የኤርትራዊነት ማንነት በጣሊያን ጌቶቻቸው አማካኝነት ለኤርትራዊያን የተሰጠ የሚኮሩበትና ለሰላሳ አመታት ያህል “ከኢትዮጵያ ቅኝ አገዛዝ ነጻ ለመውጣት” በሚል ደማቸውን እስከማፍሰስ የደረሱለት አዲስ የባርነት ማንነት ነው:: ዛሬ ይህ ተገኘ የተባለው “የኤርትራ ነጻነት” ኤርትራዊያን የአንድ ወቅት ተወዳጅ መሪያቸው ኢሳያስ አፈወርቂ ጥሰው ለማለፍ የሚሞክሩ ስደተኞች በጥይት እንዲቆሉ የሚደነግግ ፖሊሲ ባጸደቀበት የኢትዮ-ኤርትራ ድንበር ላይ ቆመው ፖሊሲውን ያለማንገራገር በሚገባ እያስፈጸሙ የሚገኙ ታማኝ ወታደሮቹን መአት በተአምር እያመለጡ ወደቀድሞ “ቅኝ ገዣቸው” ኢትዮጵያ በገፍ የሚነጉዱበት “ንጻነት” በመሆን ተደምድሟል:: ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በተዋሃደችበት ማግስት አማራውን የጥላቻ ኢላማ አድርገው የተነሱት የዚህች የቀድሞዋ የጣሊያን ቅኝ ተገዥ ኤርትራ የተማሩ ልጆች ነበሩ:: “የአማራ መንግስት” በሚሉት የሃይለ ስላሴ ስርአት ለተቀሩት የኢትዮጵያ ግዛቶች በተለይ እነሱ በስርአቱ ተጠቃሚነት በሃሰት ለሚወነጅሏቸውና በተማሪው እንቅስቃሴ ውስጥ በአብዮታዊ ተራማጅነት ስም የጸረ አማራ የጥላቻ አመለካከታቸውን ለመግፋት በመሳሪያነት ለተጠቀሙባቸው፣ ባብዛኛው የአማራ ተወላጆች ሰፍረው የሚገኙባቸው ለመሃልና የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች የተነፈጉ፣ በሃገሪቱ ምርጥ የሚባሉ በጥራትና በብዛት እጅግ የላቁ የትምህርት ተቋማት ተገንብተውላቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በመደረጋቸው የወቅቱን የሃይለ ስላሴ ዩኒቨርሲቲ በገፍ መቀላቀል የቻሉት የኤርትራ ብሄርተኞች ነበሩ:: በግዜው የተራማጅነት ጭምብልን አጥልቀው የነበሩት የትግሬ ልሂቃንም እንዲሁ በማርክሲዝም ርዕዮተ አለም ስም የጸረ አማራ አመለካከትን ማስፋፋት ችለው ነበር:: ይህ የተራማጅነት ጭምብል ባለፉት 23 አመታት ዛሬ “ጉዳዬ ሞላ” የሆነላቸው የትላንቶቹ ተራማጅ ትግሬዎች (የኢህኣፓ፣ የመኢሶን፣ የኢሰፓ አባላት የነበሩ)ያለአንዳች ይሉኝታ ከፋሺስቱ የወያኔ ትግሬ መንግስት ጋር መሰለፍን በመረጡበት ወቅት ሙሉ ለሙሉ ሊጋለጥ ችሏል:: ምክንያቱም የትግራይ ተወላጆች በወቅቱ ይታገሉለት የነበረው አላማ የሃገሪቱን ህዝቦች በእኩል ተጠቃሚ የሚያደርግ ዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለመገንባት ሳይሆን የአማራን መንግስት ለመጣል ነበር:: ያልጠረጠሩት የዋህ የአማራ ተራማጆች ደግሞ ይህ የተማሪው እንቅስቃሴ የጸረ አማራ ስብከትና ነጋሪት ጉሰማ በወቅቱ ወዴት እያመራ እንደነበረ ለማወቅ የሚያስችል ግንዛቤ አልነበራቸውም:: ቢያንስ ባለፉት 58 አመታት ውስጥ የአማራው ወጣት አማራውን በጨቋኝነት፣ በደም መጣጭነት፣ በነፍጠኛ ወራሪነት ወዘተ የሚወነጅል ልብወለድ ያለመታከት በመሰበኩ ትክክል ነው ብሎ ተቀብሎ ከማንነትቱ ጋር እንዲያዋህዳቸው ተደርጓል:: ነፍጠኛ የሚለው ቃል ብሄርተኞች አማራ ለማለት የሚጠቀሙበት ምትክ የ“ኮድ” ቃል ሲሆን ምንም እንኳን በግዜው ብዙ ነፍጠኞች አማራ የነበሩ ቢሆንም ነፍጠኝነት ከአንድ ጎሳ ማንነት ጋር የተያያዘ ባህሪ እንዳለመሆኑ መጠን አንድን የኢትዮጵያ ጎሳ ብቻ ሊወክል እንደማይችል ከሚቀጥለው ምሳሌ መረዳት ይቻላል:: ኢትዮጵያዊው የታሪክ ምሁር ሽፈራው በቀለ በዚህ ርዕስ ዙሪያ በሲዳሞ ክፍለ ሃገር ሰፍረው የነበሩ ነፍጠኞችን አስመልክቶ የማክሌላንን “State Transformation & National Integration: Gedeo and the Ethiopian Empire”, East Lansing, Michigan 1988)የተሰኘ መጽሃፍ ጠቅሰው የሚከተለውን ምልከታ አድርገው ነበር:
“ማክሌላን በናሙናነት የወሰዳቸው ሰፋሪዎች በሰጡት መረጃ መሰረት የእያንዳንዳቸው የጎሳ ተዋጽኦ ከመቶ እጅ ምንያህሉን እንደሚይዝ የሚያሳይ አሃዝ የጦር አበጋዞች፣ ተራ ወታደሮች፣ ሲቪሊያኖች በሚል ከፋፍሎ እንደሚከተለው አስፍሮልናል(እኛ አጠቃላይ የጎሳ ተዋጽኦ አሃዙን እንመለከታለን):- ሸዋ 69%፣ ጎጃም 12.05%፣ ወሎ 5%፣ ትግሬ 4%፣ በጌምድር 2.03%፣ እና ሌሎች 7.5%:: ለሸዋ የተሰጠው አሃዝ ሸዋ ኦሮሞዎችን፣ አማሮችን እንዲሁም ጉራጌዎችን የሚያካትት እንደመሆኑ የተፈለገውን የጎሳ ተዋጽኦ ምስል አይፈጥርም:: ለምሳሌ ያህል በሲዳሞ ሰፍረው ከነበሩ ሰፋሪዎች ውስጥ በዛ ያለ እጅ የሚይዙት በአብዛኛው ኦሮሞና ጉራጌ የነበሩ የደጃች ባልቻ አገልጋዮችና ወታደሮች ናቸው:: ስለዚህ የሸዋ አማራ ተወላጆች ተዋጽኦ እዚህ ሰፍሮ ከሚገኘው አሃዝ እጅግ ያነሰ መጠን እንደነበረው ጥርጥር የለውም::” (ለዝርዝሩ, የፕሮፌሰር ሽፈራውን: “An Economic History of Ethiopia” የተሰኘ መጽሃፍ ገጽ 104ን ይመልከቱ)።
ስለዚህ በአዝጋሚ ሁኔታ ነገር ግን በእርግጠኝነት የአማራው ወጣት የነገዱን በጎ ታሪክና አስተዋጽኦ በማደብዘዝ ከማንነቱ ጋር እንዲያያዙ የተደረጉና የወቅቱ የነገዱ መገለጫ ለመሆን የበቁ እንደ ነፍጠኛና ሌሎችም በጥላቻ የታጨቁ ማጥላያዎችን እንዲቀበልና እንደ መጥፎ ነገር እንዳይመለከት ተደርጓል:: ይህ የአማራው ወጣት ለረጅም ዘመን ሰለባ የተደረገበትና እራሱ ዋነኛ የማራጋቢያ መሳሪያ በመሆን የሚገፋው አዝጋሚ ጸረ አማራ የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ውርጂብኝ የአማራውን ወጣት በተለይ ተማረ የሚባለውን ልሂቅ ማንነትን አበሻቅጠውና አጨቅይተው የሚያስነውሩ፣ በነገዱ ላይ የሚወረወሩ ርካሽና ጸያፍ የጥላቻ ቅጽላዎችን አሜን ብሎ በተቀበለበት ደረጃ እንዲዘቅጥ አድርጎታል:: ይህ ለረጅም ዘመናት በተሰላና በተቀነባበረ መልኩ የተገፋው የአማራውን ህዝብ ማንነት የማስነወር አዝጋሚ ሂደት በግዜ እየተከማቸና እየተደራረበ መጥቶ ሰለባ ያደረጋቸውን የአማራ ተወላጆች ከጎሳ ማንነታቸው ጋር የተሰፉላቸውን የሃሰት የስም ማጥፊያ ስያሜዎች በሙሉ ትክክል ነው ብለው የተቀበሉበት ደረጃ ላይ አድርሷቸዋል:: ዛሬ የዚህ ትውልድ አባል የሆነው የአማራው ልሂቅና ወጣት አማራው በታሪክ ኢትዮጵያ ላይ ለደረሱ ውድቀቶች ሁሉ ተጠያቂ መሆኑን አምኖ በመቀበሉ ከተከፈተበት ማንነቱን የወንጀለኝነትና የአረመኔነት ገጽታ የሚያላብሱ የፕሮፓጋንዳ ጦርነቶች እራሱን ለመከላከል ሙሉ በሙሉ ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል::
ዛሬ አማራው እራሱን መከላከል በማይችልበት ደረጃ እንዳይላወስ ተደርጎ ስነልቦናው ሽባ የተደረገበት ሁኔታ የስነ አእምሮ ምሁራኖች በእንግሊዘኛው “ኢንተርናላይዜሽን” (Internalization) በማለት የሚገልጹት የስነልቦና ለውጥ ሂደት አይነተኛ መገለጫ ነው:: ይህ ሂደት የአማራው ልሂቅ በጠላቶቹ የተጫነበትን አሉታዊ የማንነት መገለጫዎችን እንዲቀበል የተደረገበትን ምክንያት ይገልጽልናል:: የሚሰራው ነገር ሁሉ መጥፎ እንደሆነ በወላጆቹ ወይም በአሳዳጊዎቹ ዘወትር የሚነገረውና ሁሌ ግዜ የሚገረፍ ልጅ በግዜ ሂደት የእውነትም መጥፎ ልጅ እንደሆነ ማመን ይጀምራል:: በተመሳሳይ ሁኔታ ሰዎች ምንም እንኳን ስብእናቸውን የእውነት የማይገልጹ ቢሆኑም በተደጋጋሚ ከሌላ አካል ለሚሰነዘሩ ማንነታቸውን ጥላሸት የሚቀቡ ዘለፋዎች ተጋላጭ ሲደረጉ በሂደት እነዚህን ዘለፋዎች ትክክለኛ የማንነታቸው መገለጫዎች አድርገው መቀበል ይጀምራሉ:: “ኢንተርናላይዜሽን” በማለት የምንጠራው እንዲህ ያለውን አሉታዊ የስነልቦና ለውጥ ሂደት ነው:: ወደ አማራው ልሂቅና ወጣት ስንመለስ ደግሞ ማንነቱ በደም መጣጭነት፣በጡት ቆራጭነት፣ በበዝባዥነት ፣ በባሪያ ፈንጋይነት፣ በወራሪነት ወዘተ አሉታዊ ገጽታዎች የተተካበትን ሁኔታ አሜን ብሎ የተቀበለበትን ሂደት ያስረዳልናል:: በዚህ አይነት ዛሬ ከ23 አመታት የወያኔ ትግሬ ናዚያዊ አገዛዝ በኋላ የአማራው ህዝብ እራሳቸውን “የጭቁን ጎሳዎች ተወካይ” ብለው በሚጠሩ፣ የአማራውን ምስኪን ገበሬ እንዳሻቸው መስደብ፣ ማዋረድ፣ለከፋ እንግልት መዳረግ፣ ማፈናቀል፣ ማሳደድ፣ መጨፍጨፍ የሚያስችል መብት ባለቤቶች እንደሆኑ በሚሰማቸው የጥላቻ አሻሻጭ ብሄርተኞች የሚተላለፍበትን ማንኛውም አይነት ፍርድ ያላንዳች ይግባኝ መቀበል የሚገባው ከሰብአዊ ፍጡርነት በታች ወርዶ እንደ አውሬ እንዲታይ የተደረገና ህልውናው ከፍተኛ ጥያቄ ውስጥ የገባ ማህበረሰብ ለመሆን በቅቷል:: ምክንያቱም እንዲህ እንደ አደገኛ አውሬ እንዲቆጠር የተደረገ እንደ አማራው ያለ ማህበረሰብ ምንም አይነት የዜግነት መብት ስለማይኖረው እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ሊደረግለት የሚገባው አይሆንም:: ስለዚህ የአማራው ህዝብ በደል የሚገባውን ያህል አትኩሮት አለማግኘቱ የሚያስገርም ነገር አይደለም:: በአንድ ወቅት ብቻ 78,000 አማሮች ከደቡብ ኢትዮጵያ ሃብት ንብረታቸውን ተነጥቀው አራስ ልጆቻቸውን እንደያዙ ሲባረሩ አብዛኞቹ ነጻ ሚዲያዎችና ድህረ-ገጾች ለጉዳዩ የሚዲያ ሽፋን ላለመስጠት የወሰኑበት ክስተት እዚህ ጋር ተጠቃሽ ነው:: በዚህ አይነት እንደ ብሄራዊ ጨቋኝነት፣ ደም መጣጭነት፣ ወራሪነት፣ ስግብግብ በዝባዥነት፣ ተስፋፊነት፣ጨፍጫፊነት፣ ጡት ቆራጭነት ያሉ አሉታዊ ታሪኮች ውጪ በጎ አስተዋጽኦ ለሌለው አረመኔ ማህበረሰብ ስቃይና መከራ የሚቆረቆርና ግድ የሚለው ሰው አይኖርም:: በተመሳሳይ እንደ ወያኔ ባሉ የጎሳ ብሄርተኞች የጥላቻ ስብከት ማንኛውም አይነት ሃዘኔታና ርህራሄ የማይገባው አውሬ ሁኖ እንዲታይ የተደረገው አማራ ዛሬ በጎሳ ልሂቃኖች፣ የብሄርተኛ ድርጅቶች ደጋፊዎችና የአማራውን መበደል እንደ አንድ የተለመደ ተራ ነገር የቆጠሩት የራሱ የአማራ ልሂቃኖች ጭምር በቂም በቀል፣በጥላቻና፣ በቸልተኝነት ስሜት መታየቱ የሚያስገርም ነገር አይሆንም::
ሰሞኑን በECADF ፓልቶክ ክፍል ውስጥ አንድ ነጠላ ዘፈን ተለቆ ነበር።
የድምጽ ቀራጯም በፓልቶክ ስሟ ሙያዬ ምስክር ተብላ የምትጠራ ሲሆን ትክክለኛ ስሟ ሙሉ ወንድም አገኘሁ ይባላል።ይቺ ሴት የአማራዎች ከጉራፋርዳ መፈናቀል ያስከተለው የአማራ ብሄረተኝነት መነቃቃት ክፉኛ ካስደነገጣቸው የግንቦት ሰባት አጨብጫቢዎች ዋናዋ በመሆኗ ነው።አማራ የሚባል ዘር የለም እስከማለት ርቀት ሄዳ እሷና መሰሎቿ በሚቆጣጠሩት ፓልቶልክ ክፍል ውስጥ እንደነፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪኣምና ነብሳቸውን ይማረውና ዶክተር ማይገነት አይነቶቹን እንግዶች እየጋበዘች የአማራን ህልውና የክህደት መልክቷን ለመሸጥ በጣም ጥራ የነበረ ቢሆንም ቅሌትን ከማትረፍ ውጪ ምንም ሳታተርፍ በመቅረቷ ተልኮዋን ባለማቋረጥና ማሳደዷን በመቀጠል፤የአማራው በሃገሪቷ አራቱም ማእዘን መሳደድና መገደል ቁጭት የወለደውን ሞረሽ ወገኔን ማብጠልጠሉን ስራዬ ብላ ለረጅም ጊዜ ተያይዛዋለች፤የዚሁ የጠላትነቷ ጉዞ ቀጣይ የሆነው አካል ነበር በሷ አጠራር “አርበኛ”ነዐምን ዘለቀን ጋብዛ መነሻውን ስለሰሞኑ የወያኔና የሻቢያ አደናጋሪ ግርግር ጉዳይ ጠይቃው እሱም ለሻቢያ ያለውን የታማኝነት ጥልቀት ሲደሰኩር ውሎ በመቀጠልም የዚሁ ኢንተርቪው ዋናው አካል የሆነው በመጨረሻ የጠየቀችው ጥያቄ ነበር አስገራሚው ጉዳይ።ያም ጥያቄ ከታች የለጠፍኩት የግንቦት ሰባት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የዘር ስብጥርን አስመልክቶ በአሽሙር መልክ እንዲያውም “አሉባልታ”የሚል ስም ሰጥታው፤”እውነት ነወይ ግንቦት ሰባት የደቡቦች ነው”እየተባለ በአማራ ስም የተደራጁ ቡድኖች የተሰጠው ስም ብላ ነበር የጠየቀችው፤እሱም ያው ታውቁታላችሁ የፈለገውን እንዲናገር ተፈቅዶለት ተሞላቆ ያደገ ልጅ ነበር መሰለኝ አንዳንድ ጊዜ አደባባይ ላይ መውጣቱን ይረሳውና የሚሳደባቸው ስድቦች እንደሱ ላሉ ሊሸከማቸው የማይችላቸውን ስልጣናት ተሸክሞ የማይገባና ጸያፍ በሆነ ቃል ነበር የሞረሽን ሰዎች ሲዘልፍ የተስተዋለው።
እታች የተገለጹት የድርጅቱ ስራ አመራሮችን ከአማራ የጸዳ ነው መባሉን ሽምጥጥ አድርጎ ክዶ ለምሳሌነት ስለራሱ ሲናገር እናቴ ሙሉ በሙሉ አማራ ነች ብሎ ሲል ጠያቂዋም እናቱን እንደምታውቅ ነግራው የእምነት ክደት ትርእይቱ ተባባሪ ለመሆን ሞክራለች።በመቀጠልም “አርበኛ”ነዐምን አባቱም ባባቱ አባት ወገን ነው እንጂ ኦሮሞነቱ በእናት አማራ እንደሆኑና እንዲያውም ሃረር ውስጥ ነፈጠኛ ቤተሰብ ተብለው ከሚጠሩ ወገኖች አካል እንደሆኑና እሱም የአማራው ጎኑ ተደምሮ ሲቀነስ 3/4ኛ እንደሆነ ደስኩሮልናል።”የሰውን ማንነት ለማወቅ ከፈለግህ ከነማን ጋር እንደሚውል ካየህ ወይም ከረጅም ንግግሩም ጭምር ተነስተህ ልትረዳ ትችላለህ”እንዳለው ብሂሉ፤አባቱም ኮማንደር ዘለቀ በኤርትራ ውስጥ 40 አመት በኢትዮጵያ ባህር ሃይል አዛዥነት እንደሰሩ ነግሮናል።ሁላችንም እንደምናውቀው ባህር ኋይሉ ባሳፋሪ ሁኔታ በሻቢያ ተዋርዶ ተደምስሷል።ታዲያ የኝህ ሰው ልጅ ለሻቢያ እንዲህ የሚያንገበግብ ፍቅር ከምን የመነጨነው የሚል ጥያቄ አጫረብኝ።ነገሩ ግር የሚያሰኝ ብቻ ሳይሆን ለማንም ራስ የሚያሳክክ ነገር ነው።
አባቱ የኢትዮጵያን ባህር ሃይል አዛዥ ሆነው 40 አመት ሙሉ ሻቢያን ሲያስጨንቁ ነበር ወይስ ሲጨነቁለት ነበር የኖሩት የሚል ጥያቄም ያስነሳል። ምክንያቱም ሁላችንም እንደምናውቀው ኢሳያስ አፈወርቄ የሚባል ሰው በጣም ቂመኛ ሰው እንደሆነና እንኳን የኢትዮጵያ ወታደር አዛዥ ሆኖ ሲያስወጋው የኖረን መኮንን ቤተሰብ ይቅርና ከአማራ ተራ ወታደርና ከኤርትራዊት ሴት የተወለደችን የ2 አመት ህጻን ልጅ ከነእናቷ ጋር ከኤርትራ መሬት ያባረረና ይህንንም ትእይንት በዚያን ወቅት የአለም ቀይ መስቀል ጉድ ብሎ የዘገበው ጉዳይ ከመሆንም ባሻገር፤የኤርትራና የትግሬ ዝርያ የሌላቸውን ምርኮኛ ወታደሮች በሙሉ እጃቸውን በሰላም ከሰጡ በኋላ እረባዳ ቦታ አስወስዶ በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎቻችንን በአሰቃቂ ሁኔታ ያስረሸነ አረመኔን ሰው ፍቅር ነዐምን የኮማንደር ዘለቀ ልጅ በምን ድግምት አገኘው?ይህን ጥያቄ አንባቢውም ይወያይበት።
“አርበኛ” ነዐምን ትረካውን በመቀጠል ስለብርሃኑ ነጋ ጉራጌነት ነገረንና የሌሎቹን አድበስብሶ ነው ያለፈው፤አልጨረሰውም፤ስለዶክተር ታደሰ ብሩ፤ስለሙሉነህ እዩኤል፤ስለ የምኒሊክ ተሳዳቢው ኤፍሬም ማዴቦ ምንነት አልነገረንም።
እነዚህ ሰዎች አይደሉ እንዴ ቁልፍ የግንቦት ሰባት አመራሮች?እኛ ችግራችን የደቡብ ሰውነታቸው አይደለም፤ችግሩ ዘረኝነታቸው ነው።እኔ የዚያ ፓልቶልክ አድሚን በነበርኩ ጊዜ አንድ የተከሰተ ነገር ልንገራችሁ፤እሁድ ቀን ይመስለኛል ውይይት እያካሄድን እያለን አንድ ታዳሚ ማይክ ያዘና ሎሳንጀለስ ከተማ ውስጥ አንድ አስቂኝም አስደንጋጭም ክስተት መከሰቱን ነገረን፤ነገሩም እንዲህ ነው:
የሎሳንጀለስ አካባቢ የግንቦት ሰባት አባላት ስብሰባ ተጠርተው ውይይት ከተጀመረ ከኋላ ድርጅቱን የሚመሩ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ቤቱ እንዲመርጥ ለስብሰባው ጠሪዎች ከተሰብሳቢው ጥያቄ ሲቀርብላቸው፤ምርጫው ከስብሰባው በፊት እንደተጠናቀቀ ስብሰባ ጠሪዎቹ ይናገራሉ፤ታዳሚውም መልሶ ማን መረጣቸው ብሎ ላነሳው ጥያቄ መልሱ አጭርና ግልጽ ነበር “የበላይ አካል የድርጅት ክፍል ሃላፊ”የሚል ነበር መልሱ፤ያ ሰው ደግሞ ሙሉነህ እዩኤል ነበር፤የሚገርመውና አይናችንን ያበራው ጉዳይ በበላይ አካል ተወክለዋል የተባሉት ሁሉም የደቡብ ተወላጆች መሆናቸው ነበር።ማይክ ይዞ ይህንን ፈንጂ ያፈነዳውን የሎስንጀለስ ልጅ እነሙያዬ አስቆሙትና ከክፍሉ አስወጡት።በዚያ ጉዳይ ላይ ቤቱም እንዲወያይ አልተፈቀደለትም ነበር።ከዚን ጊዜ ወዲህ ያ ጦሰኛ ልጅ ወደዚያ ክፍል አልተመለሰም በቋሚነት ታግዷል(ባን ይሉታል በእንግሊዘኛ)።
ይህ ፖልቶክ ክፍል ማለትም ECADF ለግንቦት ሰባት ከኢሳት ቴሌቪዥን የማይተናነስ አገልግሎት የሚሰጥና አብዛኞቹ የድርጅቱ አባላት የሚታደሙበት ክፍል በመሆኑ ያ ክስተት ትልቅ አቧራ በማስነሳቱ እነ ብርሃኑ ነጋ ተደናግጠው ሙሉነህ እዩኤልን ከድረጅት ጉዳይ ሃላፊነት ባስቸኳይ አነሱት።እንደፈሩት እኛም ከዚያን ቀን ጀምሮ የየአካባቢያችን የግንቦት ሰባት ተጠሪዎችን መመርመር ስንጀምር ውነትም ተሰብሰበን የመረጥናቸው አይደሉም የድርጅቱ ተወካይ ሆነው የሚመሩን፤ከበላይ አካል የተወከሉ ኖረዋል፤አሁንም እነሱው ናቸው እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ድርጅቱን የሚመሩት፤የደቡብ ልጆች።ሌላም ሌላ ማለት ይቻል ነበር ስንቱ ተወርቶ ያልቅል እንጂ።እንደኔ አይነቱን በምኖርበት አካባቢ የነሱን ሰው እስኪያገኙ ድረስ ያስቀምጣሉ እንጂ እምነት አይጣልባቸውም፤በአንድ ወቅት ስንት ደክሜ ለድርጅቱ መልምዬ ያቀረብኩላቸውን ሰዎች አንቀበል ብለውኝ ወትውቼ ሲያቅተኝ ሙያዬ ምስክርን ራሷን ወደ አለቃዬ አማላጅ ብልክም አልሆን ብሎኝ የሙሉነህ እዩኤልን ስልክ ቁጥር ከሷ ተቀብዬ ደውዬ አግኝቸው ስለችግሩ አነጋግሬው የሰጠኝ መልስ የሚገርም ነበር፤እኔ ምንም አያገባኝም እዚው ጨርስ ነበር ያለኝ።የኔ አካባቢ የአህጉሩ ተጠሪ የሱው አካባቢ ሰው ስለሆነ ለሱው መልሶ ሰጠኝ።ያቺ ቀን ነበረች ከዚህ ጉደኛ ድርጅት የተገላገልኩባት ቀን።ትእቢታቸው እስከዚህ ድረስ ጣሪያ የነካ ነበር።ያን ያህል ተዋርደን በትክክል ምሩን ነበርን ያልናቸው እኛ የአማራ ልጆች፤እነሱ ግን እኛን መግፋቱን ቀጠሉበት።ይህ ነው ሃቁ።
በተረፈ የአማራ ልጅ የሆንክ ሁሉ የየራስህን ምርምር አካሂድ ምን እየተሰራ እንደሆነ በዚሁ ጉደኛ ድርጅት ዙሪያ።ለማጠቃለል ያህል።ይህን አስቀያሚ የዘር ቆጠራና መሰሪ አካሄድ የጀመረው ዘረኛው የግንቦት ሰባት አመራር አካል እንጂ እኛ አይደለንም።እኛም በየዋህነት ልንከተላችው ያሉትን ሁሉ እስከ ህይወታችን መገበር ድረስ ርቀት ሄደን ዋጋ ልንከፍል የተዘጋጀን የዘረኝነት ጋኔል እንደነሱ ያልጠጠናወተን ንጹህ የኢትዮጵያ ልጆች ነበርን።እዚህ የዘቀጠ ጨዋታ ውስጥ ያስገቡን እነሱው ናችው።
ተገፍተን ገደል ሊከቱን አፋፉ ላይ ስለደረስን እነሱ የወረዱበት ወርደን ራሳችንን ማዳን የግድ ይላል።አለበለዚያ መጥፋታችን ነው።የአማራ ልጅ ጀንበር ሳይጠልቅ ራስህን ለማዳን ተንቀሳቀስ፤ገፉን እንጂ አልገፋናቸው።
“ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር”

No comments:

Post a Comment

wanted officials