Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, November 24, 2015

ሁለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኃላፊዎች በሙስና ተጠርጥረው ተከሰሱ

CBE SA.png
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅና የደንበኞች አገልግሎት መኮንን፣ በሥልጣን ያላግባብ የመገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ጥቅምት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመሠረተባቸው፡፡
የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተባቸው ሶስና ሀዲስ ገበየሁ (የደንበኞች አገልግሎት መኮንን)፣ አቶ ጌታቸው ዋቅሹም (የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ በተጨማሪም በደቡብ ክልል መንግሥት ኦዲት ቢሮ የመዝገብ ቤት ሠራተኛ አቶ ፀጋዬ ግርማ ሲሆኑ፣ ክሱ የቀረበው ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ነው፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በጥቅም ተመሳጥረውና ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመገልገል፣ የባንኩ ባልደረባ የሆኑት ወ/ሮ አለፊያ ከድር ለቤት መግዢያ ባንኩ የፈቀደላቸውን 320,000 ብር ለግል ጥቅም ማዋላቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡
ተከሳሾቹ ባንኩ ለግለሰቧ የፈቀደውን ገንዘብ ቤቱን የሸጡላቸው ወ/ሮ ፅጌረዳ ሰይፉ አካውንት ማስገባት ሲገባቸው፣ በሁለተኛ ተከሳሽ ፀጋዬ ግርማ አካውንት ውስጥ በማስገባትና በተለያዩ ጊዜያት እያወጡ መጠቀማቸውም በክሱ ተገልጿል፡፡
የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ዋቅሹም፣ ገንዘቡ ለወ/ሮ ፅጌረዳ ሰይፉ ገቢ መደረጉን ሳያረጋግጡ በማፅደቃቸው፣ ከባድ ጉዳት በማድረስና ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት ወንጀል ተከሰዋል፡፡ አቶ ጌታቸው የተጠረጠሩበት ወንጀል ዋስትና እንደማያስከለክል ተገልጾ፣ በ3,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱ በማዘዝ ለኅዳር 21 ቀን 2008 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
Source: Reporter Newspaper

No comments:

Post a Comment

wanted officials