Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, November 8, 2015

ትህዴን በአስመራ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ማስመረቁን አስታወቀ








የሕወሓት መንግስት ሞላ አስገዶምን አስኮብልሎ ወደ ኢትዮጵያ ካስገባ በኋላ ካሁን በኋላ ትህዴን የሚባል ድርጅት አስመራ ውስጥ የለም ሲል ፕሮፓጋንዳ ሲነዛ ቢቆይም አስመራ የሚገኘው ትህዴን አዳዲስ ምልምል ወታደሮችን ማስመረቁን አስታውቋል::

የትህዴን ድምጽ እንደዘገበው የትህዴን ማሰልጠኛ ክፍል ሰልጣኝ አሰር የሚል ስያሜ ተሰጥቷቸው ለበርካታ ወራት በወታደራዊ በፓለቲካዊ በማሰልጠኛ የቆዩትን በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰልጣኝ በጥቅምት 20 /02/2008 ዓ/ም የበላይ ሃላፊዎች፥ ወታደራዊ አዛዥ የትህዴን ደጋፊና ወንድማዊ ድርጅቶዎች እንዲሁም የትግል ደጋፊ በተገኙበት እንግዶዎች በደመቀ ሁኔታ አስመርቋዋል።
በዚህ ምረቃ ላይ የተገኙ የትህዴን የበላይ አመራር መኮንን ተስፋየ ባሰሙት ቃል አንዳንድ ወላዋይ የሆኑ ታጋዮች የትግል መሰመር እየለቀቁ ቢሂዱም የትህዲን ድርጅት ትግል ግን በተቃራኔው በወታደራዊ በፓለቲካዊ አቅም በመጠናከር ወደፊት በመገስገስ ላይ እንደሚገኝና እንዲዚሁም በመቶዎች የሚቆጠሩ አሰር ተመራቂዎች በቂ እውነተኛ ምስክር መሆናቸውን በንግግራቸው ባሰሙበት ወቅት ገልፀዋል።

ይህን ብአል ለማድመቅ የሚያስፈልጉ ነገሮች አዘጋጅተው የተገኙ የትህዴን የባህል ቡድን በተለያዩ የአገራችን ቋንቛዎች በተዋሃዱ ዜማዎችና ድርማዎች ይዘው የቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም ሌሎችም ዝግጅቶዎች ጨምረው ለተመራቂ ሰልጣኞዎች በደመቀ ሁኔታ አቅረበዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials