Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, October 30, 2014

ስብሰባው ቅዱስ ሲኖዶሱን ልዕልና በማጽናት ተጠናቀቀ፡፡ የፓትርያርኩ ምሬትና ብስጭት ያሳሰባቸው ብፁዓን አባቶች ሲያረጋጓቸው አመሹ

የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያው የቅዱስ ሲኖዶሱን ልዕልና በማጽናት ተጠናቀቀ፤ የፓትርያርኩ ምሬትና ብስጭት ያሳሰባቸው ብፁዓን አባቶች ሲያረጋጓቸው አመሹ


His Holiness Abune Mathias with thier Graces the Archbishops
  • ‹ከሕዝብ አጋጫችኹኝ፤ ከወንድሞቼ አንድነት ለያችኹኝ፤ ከነገራችኹኝ አንዱንም የተቀበለኝ የለም›› በሚል የተመረሩት አቡነ ማትያስ ምክራቸው ያልሠመረላቸውን ሦስት አማሳኝ አማካሪዎችን በከፍተኛ ድምፅ ‹‹ውጡልኝ›› በማለት ከፊታቸው አበረሯቸው፡፡
  • ከትላንትናው የስብሰባ ውሎ መጠናቀቅ በኋላ ፓትርያርኩ የነበሩበት የምሬትና የብስጭት ኹኔታ ተነግሯቸው ወደማረፊያቸው የተጠሩት በሹመት ቅድምና ያላቸው ብፁዓን አባቶች÷ አቡነ ማትያስ በተጠሪነት ጉዳይ የተሟገቱለት አቋም የቤተ ክርስቲያን እንዳልኾነ፣ ለአጭር ዕድሜ የኖረው የቤተ ክርስቲያን ሕግ መለወጥ እንደሌለበት ይልቁንም የአማሳኞችንና የባዕዳንን ምክር ከመስማትና ከመቀበል ተጠብቀው ትላንት ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጋራ ኹነው የተከላከሉለትን ሕገ ቤተ ክርስቲያን ማስከበራቸውንቢቀጥሉ በእርሳቸውና በአባቶች መካከል ያለው ውጥረት ሊረግብና ሊተራረቅ እንደሚችል አመልክተዋቸዋል፡፡
  • ፓትርያርኩ በትላትናው ምሽት አማሳኞቹን በብስጭትና በምሬትም ቢኾን ከአበረሯቸውና በብፁዓን አባቶች ምክር ከተጽናኑ በኋላ በዛሬው የምልአተ ጉባኤው ውሎ ስብሰባውን በተረጋጋና በመግባባት መንፈስ ሲመሩና ‹‹እናንተ ካላችኁት አልወጣም›› እያሉ በጋራ ሲወስኑ ውለዋል፡፡
  • የቅዱስ ሲኖዶሱን የበላይነት(ልዕልና) በማረጋገጥ በተጠናቀቀው የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቅ አጀንዳ፣ ከፓትርያርኩ ጀምሮ እያንዳንዱ ሊቀ ጳጳስና ኤጲስ ቆጶስ(ጳጳስ) ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶሱ እንደኾነ ጸንቷል፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት ኾኖ ሲሠራበት የቆየው ልምድ በማሻሻያው ተካትቶ እንዲደነገግ ተወስኗል፡፡ በልዩነት ነጥቦቹ ላይ በተላለፉት ውሳኔዎች መሠረት ረቂቁ ተስተካክሎ ሲቀርብ በምልአተ ጉባኤው አባላት ፊርማ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል፡፡
  • በደቡብ አፍሪቃ በሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብና በምእመናን መካከል ለተፈጠረው አለመግባባት መፍትሔ ለመስጠት በቀረበው የአጣሪ ልኡክ ሪፖርት ላይ የመከረው ምልአተ ጉባኤው÷ ብፁዕነታቸው ለጊዜው መንበረ ጵጵስናቸውን በናይሮቢ አድርገው በኬንያ፣ በጅቡቲና በሱዳን ተወስነው እንዲሠሩ፤ በደቡብ አፍሪቃ ደግሞ አገልግሎቱ በአድባራት አለቆችና በሰባክያነ ወንጌል ላይ ተመሥርቶ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡ ምልአተ ጉባኤው በሰሜን አሜሪካ በሚገኙት ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ጉዳይ መምከር ጀምሯል፡፡
  • ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ራሱን የቻለ ሊቀ ጳጳስ ስለመመደብና በሀገረ ስብከቱ የተፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ በነገው ዕለት በመምከር ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials