Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, October 29, 2014

ስለ አቶ መለስ ዜናዊ ቀበቶ ያወራችው ዘፋኝ ሃይማኖቷን ቀየረች

weyso
(ዘ-ሐበሻ) አቶ መለስ ዜናዊ የሞቱ ሰሞን በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ቀርባ “አቶ መለስ ቀበቶ እንኳ አድርገው አያውቁም ነበር” በሚል ተናግራ በብዙዎች ትችት ውስጥ ወድቃ የነበእረችው ዘፋኝ ትዕግስት ወይሶ ኃይማኖቷን ቀየረች።
“ቆጨኝ” በሚል ዘፈኗ የምትታወቀውና በተለይም ስለአቶ መለስ ቀበቶ በመናገር ታዋቂነትን ያተረፈችው ትዕግስት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖቷን ቀይራ የፕሮቴስታንት ኃይማኖት ተከታይ መሆኗን አስታውቃለች። ት ዕግስት አቶ መለስ በሞቱ ሰሞን ካልጠፋ ምሳሌ ዘላ ቀበቷቸው ላይ ማተኮሯ የብዙዎች መነጋገሪያ አድርጓት እንደነበር ይታወሳል።
“ሕይወቴን ለእየሱስ ሰጥቻለሁ” ስትል ለኤፍታህ ኃይማኖታዊ መጽሔት ቃለምልልሷን የሰጠችው ትዕግስት ወይሶ ሙዚቃ ማቆሟን እና ወደ መዝሙር እንደምትገባ አስታውቃለች።
– Ze-Habesha

No comments:

Post a Comment

wanted officials