በቤንች ማጅ ዞን ጉራፋርዳ ወርዳ የአማራው እልቂት ቀጥሏል
ወደ ሀገራችሁ ሂዱ እሄ የኛ ሀገር ነው በሚል ወያኔ አሰልጥኖ ባሰማራቸው የአካባቢው ታጣቂዎች የተጀመረው እና ትናንት ከጥዋቱ 12 ሳሀት ጀምሮ የ25 ንፁሀንን ህይወት የቀጠፈው እረብሻ ቀጥሎ ዛሬም ሌሊቱን ሙሉ በተደረገ የቤት ለቤት ግድያ ሌሎች 4 ሰወች ተገድለው ፤ አንድ የ3 አመት ህፃን ከናቱ ተነጥቆ ተወስዷል : ትናንት በእረብሻው በጥይት ከተመቱት 11 ሰወች ውስጥ አቶ አሰፋ ቢለው የተባለው እና አቶ ስማቸው ካሳ ህክምና ባለማግኘታቸው ዛሬ ህይወታቸው አልፋል ።
በደቡብ ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ካለፉት ሶስት ቀናት ጀምሮ መንግስት እየተከተለ ያለው ዘርን ማእከል ያደረገ ፖሊሲ ለግጭቱ ዋናው መንስኤ ቢሆንም፣ በአካባቢው የሚታየው የመሬት ቅርምት ግጭቱ በማየሉ፣ በተለይ ሴቶችና ህጻናት አካባቢውን እየለቀቁ በመሰደድ ላይ ሲሆኑ፣ ዛሬ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የጫኑ መኪኖች ወደ አካባቢው ተንቀሳቅሰዋል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች ግጭቱ ወደ ሌሎች ከተሞች ይዛመታል በሚል በፍርሃት መዋጣቸውን ተናግረዋል::