Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, October 16, 2014

በኢትዮጵያ ተከታታይ ፍንዳታዎች ይደርሳሉ የሚለው ስጋት አይሏል

በኢትዮጵያ ተከታታይ ፍንዳታዎች ይደርሳሉ የሚለው ስጋት አይሏል * ደህነቶች እና የኢምባሲ አታሼዎች በስብሰባ ተወጥረዋል

  • 1339
    Share
በኤምባሲዎች የደህንነት አታቼዎች እና በወያኔ የደህንነት ባለስልጣናት መካከል ስብሰባ እየተካሄደ ነው።
ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው 
በኢትዮጵያ ውስጥ ተቀማጭነታቸውን ያደረጉ ምእራባውያን ዲፕሎማቶች ዘንድ የሚደርሱ እናፈነዳለን መረጃዎች ከፍተኛ የሆነ ስጋት እየፈጠሩ መሆኑን በአዲስ አበባ የሚገኙ እና ለደህንነት አታቼዎች ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገልጸዋል።
addis-ababa-realethiopia-141
ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ሰዎች እንደሚናገሩት መሃል አገርን እና ምስራቅ ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪት ክልሎች ይደረጋሉ የተባሉ ፍንዳታዎች ከአልሸባብ የመጡ ማስጠንቀቂያዎች ናቸው ቢባልም በአልሸባብ ውስጥ በተደረገ የመረጃ ማጣራት አልሸባብ ይህንን መረጃ እንዳልበተነ በአዲስ አበባ የአሜሪካን የደህንነት አታቼ ለማረጋገጥ ያደረጉት ሙከራ በከፊል ባይሳካም የሁኔታውን አሳሳቢነት አስመልክቶ በምእራባውያን የኤምባሲ ዲፕሎማቶች የደህንነት አታቼዎች እና በወያኔ የደህንነት ባለስልጣናት ጋር ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል።
ከወያኔ የደህንነት ባለስልጣናት ጋር ይደርሳሉ የሚባሉ ፍንዳታዎች ምዕራባውያን ላይ ያነታጠሩ በመሆኑ የሰጉት የሃያላኑ ዲፕሎማቶች ሁኔታው ከመከሰቱ በፊት ለመቆጣጠር ሲሉ አስፈላጊውን የዲፕሎማቲክ ሩጫ እያደረጉ መሆኑ ሲታወቅ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ከሆነ ምርጫ እየደረሰ ስለሆነ ተቃዋሚዎችንና ያልያዛቸውን ጠንካራ ሰዎች ለማፈስ ወያኔ የሚጠቀምበት ስልት ነው። ህዝቡን እያስፈራራ የውጭ አገር መንግስታትንም እንዲሁ አሸባሪ ለመዋጋት እያለ እራሱ የቀበራቸውን ፈንጂዎች ያስጮህብናል። የፈለገውንም ይገድላል። ስለዚህ ህዝቡ ነቅቶ መጠበቅ የግድ ይለዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials