Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, January 26, 2016

ዛሬ በሐዋሳ ለ6ኛ ግዜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ | #ለሐዋሳ እንጸልይ!

Awasa Ketema
(ዘ-ሐበሻ) ዘ-ሐበሻ ትናንት እሁድ በዘገበችው መሰረት ለ3 ጊዜያት የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር:: ዛሬ ከአዋሳ አካባቢ ያነጋገርናቸው ወገኖች እንደገለጹልን ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በ24 ሰዓታት ውስጥ ለ6ኛ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጡ ተከስቷል::
ይህ ዜና ከተጠናከረበት 20 ደቂቃ በፊት ለ6ኛ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጡን ያስታወቁት ዘ-ሐበሻ ያነጋገረቻቸው ወገኖች በደረሰው አደጋ በርካታ ወገኖች ወደ ሆስፒታል እንደተወሰዱ… በፎቅ ላይ የሚኖሩ ወገኖችም ወደ ምድር መወረዳቸውን ነግረውናል::
በሐዋሳ ነዋሪው በከፍተኛ ሁኔታ ተደናግጦ ይገኛል::
ለሐዋሳ እንጸልይ!

No comments:

Post a Comment

wanted officials