Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, January 14, 2016

በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞው የቀጠለ ሲሆን በሃሮማያ አና ኣምቦ ውጥረቱ ኣይሏል።

በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞው የቀጠለ ሲሆን በሃሮማያ አና ኣምቦ ውጥረቱ ኣይሏል።
- በዛሬው አለት በኦሮሚያ ክልል
የተሰበሰቡ መረጃዎች አንደሚጠቁሙት ተቃውሞዎች በየከተማው ቀጥለው ውለዋልበዚህም መሰረት በሻሸመኔ ከተማ የፕሪፓራቶሪ ተማሪዎች በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የሚደረገውን ግድያ በመቃውም በትምሕርት ቤቱ ግቢ ውስጥ ተቃውሞ ያሰሙ ሲሆን በሃሮማያ ሕወሓት በተኮሰው ጥይት ጫላ መሃመድ
ኣህመድ የተባለ ገበሬ ሲገደል በርካቶች የቆሰሉ ሲሆን በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች እና ገበሬዎች በሕወሓት ኣግዓዚ ወታደሮች ታፍሰው በደርግና ሕወሓት ዘመን ዜጎች አየታፈሱ ሲገደሉበትና በጅምላ ሲቀበሩበት ወደ ነበረው የኣድዐላ አና ሃማሬሳ ካምፕ ተግዘዋል።በነዚህ ካምፖች ከሁለት ኣመት በፊት የጅምላ መቃብር መገኘቱ ይታወሳል።
በወለጋ ሙጊ ኪራሙ ወረዳዎች ተማሪዎች ተቃውሞ ሲያሰሙ በሰሜን ሸዋ ሂድሃቡ ኣቦቴ ሰላሌ የሕወሓት ባለስልጣናት ሕዝቡን ሰብስበው ተቃውሞ
ለማስቆም ቢሞክሩም ሕዝቡ የታሰሩት ካልተፈቱ ግድያ ካልቆመ ወታደሮች ትምህርት ቤቶቻችንን ለቀው ካልወጡ ተቃውሞ ይቀጥላል ሲሉ
መልሰዋቸዋል። የኣምቦ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ለሊቱን በመፈክር ተቃውሞ ሲያሰሙ ያደሩ
ሲሆን በጠዋት ግቢውን ጥሰው የገቡ የሕወሓት ወታደሮች ተማሪዎችን ከዶርሞቻቸው በማውጣት ያባረሩ ሲሆን በኣምቦ ተቃውሞው ያገረኃል ተብሎ
ይጠበቃል።በትላንትናው አለት በማእከላዊ የማሰቃያ ቦታ ታስሮ የነበረው የኣምቦ ወጣት ኣብደታ በድብደባ ምክንያት መሞቱን ተከትሎ የኣምቦ ሕዝብ
ቁጣውን ያሰማል ተብሎ ይጠበቃል። ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

No comments:

Post a Comment

wanted officials