Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, January 13, 2016

በጥይት የተመታው ሙሽራ በሞት አፋፍ ላይ ነው። የሚረዳው ሆስፒታል አጥቷል




በሠርጉ ዕለት ዋዜማ ጭንቅላቱን በጥይት የተመታው መምህር ፍጹም አባተ በመቱ ሆስፒታል ቆይቶ ለቀዶ ጥገና ሕክምና ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተልኮ የሚረዳው አጥቷል። ጥቁር አንበሳ በበኩሉ ምንም እርዳታ ሳያደርግ ወደ አለርት ሆስፒታል ቢልከውም አልርት ሆስፒታል በተመሳሳይ መልሶ ወደ ጥቁር አንበሳ ልኮታል። ተገቢ ሕክምና የተነፈገው ፍጹም ደሙ በየዕለቱ እየቀነሰ ከመምጣቱ የተነሳ በሞት አፋፍ ላይ ነው።
ኢሳት
"በሬው ታርዶ፣ ምግብ ተዘጋጅቶ፣ ዘመድ ጎረቤቱ እየጨፈረ ነበር። ሌሊት 7 ሰዓት አካባቢ ከርሱ ጋር በስልክ አውርተን፣ 'አሁን ስለደከመኝ ልተኛ ነው' ብሎኝ ተሰነባበትን ከዚያ..."
በመንግስት ወታደሮች በሠርጉ ዋዜማ በጥይት የተመታው መምህር ፍጹም አባተ እጮኛ ወይዘሪት ፍሬሕይወት በለጠ ናት። ስለአሰቃቂው ሁኔታ ትናገራለች። አባቱም አሉ።
ኋላ ላይ ይጠብቁን
ኢሳት የሕዝብ ድምጽ!.

No comments:

Post a Comment

wanted officials