Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, April 9, 2016

በአማራው ክልል ፕሬዚዳንት ላይ ያነጣጠረ ግምገማ እየተካሄደ ነው

መጋቢት ፳፱( ሃያ ዘጠኝ ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-


 በቅርቡ በአማራ ክልል ተነስተው የነበሩትንና እስካሁንም መቁዋጫ ያልተገኘላቸውን የቅማንትና የወልቃይት ጠገዴን ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄን ተከትሎ ለደረሰው ደም መፋሰስ የክልሉን ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳጋቸውን ተጠያቂ በማድግ የህዝቡን ጥያቄ ለማፈን በመሩዋሩዋጥ ላይ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ገልጸዋል፡፡ የወልቃይት ጥያቄ የአቶ ገዱ የአመራር ችግር እንጅ የአማራ ህዝብ ጥያቄ አይደለም በሚል፣ ፕሬዚዳንቱን ከብአዴን አባላት እና ከህዝቡ ጋር በማጋጨት፣ ጥያቄው ተዳፍኖ እንዲቀር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን እነዚህ ወገኖች ይገልጻሉ፡፡ ከመጋቢት 23 ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት በሁሉም ዞኖች ሲካሄድ በሰነበተው የብአዴን የህዋስ ግምገማ ፣ ሁለት አላማዎችን ለማሳካት መታቀዱን የሚገልጹት ታዛቢዎች፣ አንደኛው፣ የአማራ መብት አልተጠበቀም፣ አማራ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገባውን ቦታ አላገኘም፣ የወልቃይት ጠገዴ፣ የሱዳን መሬትና ሌሎችም ተያያዝ ጥያቄ ያነሱ የድርጅቱን አባላት፣ በጠባነትና በተቃዋሚ አጀንዳ አራማጅነት በመክሰስ ነጥሎ ለመምታ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ የወልቃይት ጠገዴን ጥያቄ የአቶ ገዱ አንዳርጋቸው የግል አጀንዳ በተለይም ከትግራይ ክልል መሪ ከአቶ አባይ ወልዱ ጋር ባላቸው ቅራኔ የተነሳ የተፈጠረ ነው በሚል፣ጥያቄዉን ግልሰባዊ ይዘት በመስጠት፣ ህዝባዊነቱን መንጠቅ የሚል ነው፡፡ በዚህም መሰረት፣ በግምገማው ወቅት፣ የህዝብ ጥያቄዎች ናቸው በሚል የተለያዩ ጥያቄዎችን ሲያነሱ በነበሩ የብአዴን አባላት ላይ በየመድረኩ የማሸማቀቅና የማስፈራራት ስራ በመስራት አንገታቸውን እንዲደፉ ተደርጎአል፡፡ በእነዚህ አባላት ላይ በሂደት እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችልም ታዛቢዎች ይገልጻሉ፡፡ በሌላ በኩል ሆን ተብሎ በህወሃት የደህንነት አባላት እና ለህወሃት ታማኝነተን አላቸው በሚባሉ የብአዴን አባላት በተቀነባረው ስብሰባ አቶ ገዱን በስም እየጠቀሱ፣ የወልቃይት ችግር የግለሰብ ችግር መሆኑን ለማሳየት ጥረት ተደርጎአል፡፡ በግምገማዎች ላይ ሁሉ የሁለቱ ክልሎች መሬዎች ስም ሲነሳ የቆየ ሲሆን፣ የአቶ አባይ ስም እንዲጠራ የተፈለገው፣ አባላቱን ለማሳመንና ጉዳዩ ሴራ ያለበት እንዳይመስል ነው ይላሉ፡፡ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ የህዝብ ጥያቄ ሳይሆን የግለሰብ መሪዎች ጥያቄ ነው በማለት፣ ብአዴን ጥያቄው እንደማይመለከተውና ችግሩን የፈጠሩት መሪዎች መሆናቸውን በማሳየት፣ ጥያቄው ተዳፍኖ እንዲቀር ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡ የግምገማ ውጤቱ በሂደት የሚታይ ቢሆንም፣ የወልቃይት ጥያቄ እየገፋ የሚሄድ ከሆነ፣ አቶ ገዱን በማንሳት ጥያቄውን ለማዳፈን ሙከራ ለደረግ ይችላል፡፡ በዚህ ግምገማ ላይ የወልቃይት ህወሃት የወልቃይትን ጥያቄ የግለሰብ ጥያቄ አድርጎ በማቅረብ ለማዳፈን እየሄደበት ያለው ርቀት ችግሩን እንደማይፈታው ይናገራሉ፡፡ አብዛኛው የብአዴን መካከለኛና ተራ አባላት ብአዴን 25 አመታት ሙሉ የህወሃት ታዛዥ መሆኑን የሚቃወሙ ሲሆን፣ ሰሞኑን በተካደው ግምገማም ይህ ተቃውሞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍ ብሎ ተሰምቶአል፡፡ ከህወሃት ጋር ቅርብ ግንኙነት አላቸው የሚባሉት የብአዴን ከፍተኛ መሪዎች፣ ታች ያለው አባሉ እያነሳ ያለውን ጥያቄ የማደግፉና በጥርጣሬ የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ከፍተኛ አመራሩ እርስ በርስ ለስልጣን በሚያደርጉት ፉክክር፣ አንዱ ሌላውን አሳልፎ እየሰጠ መሆኑን ታዛቢዎች አክለዋል፡፡ በሌላ በኩል የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከህወሃት ጋር በእየለቱ ግጭት ውስጥ እየገባ መሆኑን ከአካባቢው የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የህወሃት ካድሬዎች የወልቃይትን የአማራ ማንነት ይደግፋሉ የሚሉዋቸውን እየተከታተሉ በማስፈራራት ላይ ሲሆኑ፣ በህዝቡ መካከል ግጭት ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት አካባቢውን አስፈሪ አድርጎታል፡፡ ህወሃት ጥያቄውን ለመመለስ እየተከተለው ያለው መንገድ አካባቢውን ወደ እርስ በርስ ግጭት እንዳይከተው የአካባቢው ነዋሪዎች ስጋታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ በሌላ ዜና ደግሞ መጋቢት27ቀን 2008 ዓም የሚከበረውን የመድሐኒዓለም ክብረበአል ለማክበር ከተለያዩ ቦታዎች ወደ ዋልድባ አብረንታንት ገዳም የሄዱ ምዕመናንን ታጣቂዎች አርማደጋ ላይ በማስቆም ከ200 በላይ የሚሆኑትን ንብረታቸውን ሙሉ በሙሉ እንደዘረፉዋቸው ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የገዳሙ አባቶች ለኢሳት ተናግረዋል፡፡ ዘራፊዎቹ 4 ሲሆኑ፣ ሁለቱ ይፈትሻሉ ሁለቱ ደግሞ ህዝቡን ያስቆማሉ ያሉት አባቶች፣ ክላሽ፣ ጩቤና ገጀራ መያዛቸውንም አክለዋል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials