Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, April 14, 2016

በደሴ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ የትግል ጥሪ ወረቀቶች ተበተኑ


ሚያዚያ ፭(አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወጣቶች ትናንት ምሽት በተለያዩ የደሴ ከተማ አካባቢዎች የበተኑት ወረቀት የከተማው ህዝብ ትኩረት መሳቡን ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወጣቶች ተናግረዋል፡፡ የትግል ጥሪ ወረቀቶች፣ ህዝቡ ለመብቱ እንዲነሳ፣ በወልቃይት ጥያቄ ዙሪያ የደሴ ህዝብ ጥያቄውን ከሚያቀርቡ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ጋር በጋራ እንዲቆም የሚያሳስቡ ናቸው፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ህዝብ በብዛት ይገኝባቸዋል በተባሉ ቦታዎች፣ በአራዳ፣ መናፈሻ፣ መላ፣ መናሃሪያ እና በዋና ዋና መንገዶች ወረቀቶች መበተናቸውንና ግድግዳዎች ላይ መለጠፋቸውን የሚናገሩት ወጣቶች፣ ጠዋት ላይ ፖሊሶች ወረቀቶችን ለማንሳት ሲረባረቡ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ወረቀቶቹ በበቂ ሁኔታ ለህዝብ ተዳርሰዋል ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት ወጣቶች፣ ዛሬ ድርጊቱን ሊፈ‹ሙ ይችላሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች እየተያዙ በመታሰር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡የጸጥታ ቁጥጥሩም ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ በመካሄድ ላይ መሆኑን አክለዋል

No comments:

Post a Comment

wanted officials