Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, April 11, 2016

Ethio Telecom to implement a software that can able to control Viber, WhatsApp and other VoIP services


Ethio Telecom to implement a software that can able to control Viber, WhatsApp and other VoIP services





Ethio Telecom will soon implement a software that can able to give him control over VoIP. According to Andualem Admassie, CEO of the telecom company, a new technology called Policy Charge and Control system (PCC) will be implemented to control VoIP services that people use via the telecom operator’s network.

“We are not saying we will ban these services. We will implement this technology so that we can control the use of these services through our network,” the CEO stated. He also said that the technology would allow the telecom company charge for the VoIP services.

Although the use of VoIP applications is not technically free as it would still require the use of an internet connection provided by the telecom monopoly, Ethio Telecom has stated that it has been losing revenue due to the applications. Services provided by applications such as Viber, WeChat and Whatsapp are popular amongst people as they are a cheaper alternative to connecting with friends and families as compared to a direct call.

Capital Ethiopia

የድምጽና ምስል ግንኙነት የሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ለመጣል እየተመከረበት እንድሆነ ኢትዮ-ቴሌኮም አስታወቀ

ኢሳት (መጋቢት 28 ፥ 2008)
ቫይበርና ሌሎች የስልክ ጥሪ አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ ክፍያን ለመጣል አሊያም ሌሎች አማራጮችን ለመጠቀም ኢትዮ-ቴለኮም እየመከረ እንደሚገኝ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አንዱአለም አድማሴ ለጋዜጠኞች አስታውቀዋል።
አገልግሎቱን የመቆጣጠር ቴክኖሎጂ እንዳለው የገለጸው ድርጅቱ ከአገልግሎቱ ባለቤቶች ጋር በመደራደር አመታዊ የትርፍ ድርሻቸው ክፍያ እንዲፈጽሙ መግባባት እንደሚቻልም አመልክቷል።
በአገልግልቶቹ መስፋፋት ከፍተኛ ገቢን እያጣ እንደሆነ የሚገልጸው ኢትዮ-ቴሌኮም አማራጮችን በማየት የተሻለውን ለመጠቀም ምክክር እየተካሄደ እንደሆነም ይፋ አድርጓል።
የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው አዲስ ሊጣል የታሰበው ክፍያ አገልግሎቱን እንዳይጠቀሙ የሚያደርግ እንደሆነና የስልክ ቁጥሮች ምዝገባውም ቁጥጥር ለማጥበቅ የታሰበ ነው ሲሉ በመግለጽ ላይ መሆናቸውን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል።
ኢትዮጵያ በኢንተርኔትና በስልክ አገልግልቶች ላይ ከፍተኛ ቁጥጥርን የምታደርግ ሃገር መሆኗን የተለያዩ አካላት ሲገልፁ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ ተግባራዊ ሊደረግ የታሰበውም አዲሱ ቁጥጥር ይህንኑ ድርጊት የሚያጠናክር እንደሆነም ተገልጿል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials