Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, August 20, 2014

የአያት ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ሰልፍ እንደወጡ ተነገረ

የአያት ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ሰልፍ እንደወጡ ተነገረ
ለ6 ቀናት መብራት የተቋረጠባቸው የአያት ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ሰልፍ እንደወጡ ለነገረ ኢትዮጵያ ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች ለ6 ብሎክ ያስፈልግ የነበረው ትራንስፎርመር ለ12 ብሎክ እንዲያገለግል በመደረጉ መብራት አጥተን ሰንብተናል ያሉት ነዋሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት በትናንትናው ዕለት መብራት ኃይል የትራንስፎርመሩ ችግር መሆኑን ተረድቻለሁ ብሎ ትራንስፎርመር ቢቀይርም ማታ ላይ የመብራት ኃይል ሰራተኛ ነን ያሉ ሰዎች ከሌሎች ሰዎች ጋር በመመሳጠር ፊውዞቹን ፈትተው ሊወስዱ ሲሊ እንደያዙዋቸው ገልጸዋል፡፡
ሁኔታውንም ‹‹ትናንትናም ሌላ ትራንስፎርመር አምጥተው ቀየሩ፡፡ ማታ ላይ ግን ተመልሰው መጀመሪያ የመጣውን ትራንስፎርመር ከሌሎች ሰዎች ጋር በመመሳጠር ፊውዞችን ለመቀየር ሲሞክሩ የብሎኩ ነዋሪዎች እጅ ከፍንጅ ይዘዋቸዋል፡፡›› ሲሉ አቶ ብርሃኑ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ ለዝግጅት ክፍላችን ደውለው ገልጸዋል፡፡
‹‹ጉዳዩን ወደ ፖሊስ በመውሰድ እስከ 5 ሰዓት ድረስ መፍትሄ እንዲሰጠን የጣርን ሲሆን የመብራት ኃይል ኃላፊ ነኝ ያሉ አቶ ኢሳያስ የሚባሉ ሰው ጠዋት መፍትሄ እንዲሚሰጠን ገልጸውልን ነበር፡፡›› ያሉት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሌላ የአካባቢው ነዋሪ መፍትሄ ባለማግኘታቸው ህዝብ መብራት ኃይል መፍትሄ እንዲሰጠው መውጣቱን ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ህዝቡ ወጥቶ ወደ መብራት ኃይል ለመሄድ እየተሰባሰበ እያለ መፍትሄ እንሰጣችኋለን ብለው የመጡት ሰራተኞች ‹‹ሌላ የምንቀይረው እቃ አለ›› ብለው መመለሳቸውንና ሌሎች አመራሮች መጥተው ማታ ሰው ደብድባችኋል፣ የመብራት ኃይል ሰራተኞች ሳይሆኑ እቃዎቹን እናንተ ናችሁ የሰረቃችሁት በሚል ህዝቡ ወንጀል እንደፈጸመና ለፍትህ እንደሚያቀርቡት መዛታቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
‹‹ማታ ህዝቡ ፊውዞቹን አስመለሰ እንጅ አልተደባደበም፡፡ ይህም ቢሆን የፖሊስ እንጅ የመብራት ኃይል ባለስልጣናት ስራ አይደለም፡፡ እንዴት ህዝብ ሌባ ይባላል›› ያሉት ነዋሪዎቹ በመብራት ኃይል ባለስልጣናት ማዘናቸውንና አሁንም መፍትሄ እንዲሰጣቸው ለመጠየቅ ወደ መመስያ ቤቱ በመሄድ ላይ መሆናቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials