Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, August 19, 2014

በማይጨው የስራ ማቆም አድማ ተደረገ

በማይጨው የስራ ማቆም አድማ ተደረገ

Aug 19,2014
(ኢ.ኤም.ኤፍ) ከአድዋ ጦርነት በኋላ ከጣልያን ጋር የተደረገው 2ኛው ጦርነት የተከናወነው በማይጨው ነበር። ይህ ሁለተኛ ጦርነት ማይጨውን ታሪካዊ ከተማ ያደርጋታል። የዚህ ከተማ ነዋሪ ራሱን የራያ ህዝብ አድርጎ ይወስዳል። ህወሃት ወያኔን ለመቀበል፤ ተቀብሎም እንደራሱ ድርጅት ሊከተለው አልቻለም። በዚህም ምክንያት የማይጨው ከተማ መብራት፣ ንጹህ ውሃ እና አስፋልት መንገድ በአግባቡ እንዳያገኝ ከተደረጉት የትግራይ ከተሞች አንደኛው ሆኗል።
ለምሳሌ ያህል ከመሃል አገርም ሆነ ከወሎ ተነስቶ ወደ መቀሌ የሚሄድ አውቶብስ፣ ወይም የጭነት መኪና ወደማይጨው ለመሄድ ፍላጎት የለውም። የዚህም አንደኛው ምክንያ የአስፋልት መንገድ እንዳይሰራ መደረጉ ነው። ከአላማጣ ወደ መቀሌ የሚወስደው አስፋልት በሚገባ በመሰራቱ፤ መኪኖች በቀጥታ ከአላማጣ ወደ መቀሌ ይሄዳሉ እንጂ፤ ወደ ማይጨው ለመግባት ፍላጎት የላቸውም። በዚም ምክንያት የማይጨው የንግድ እንቅስቃሴ ጭምር ተዳክሟል። ባለሃብቶች ከተማውን ለቀው እየወጡ ናቸው። አሁን ደግሞ በማይጨው የሚገኘው ቴክኒክ ኮሌጅ ወደ ዩኒቨርስቲነት ከፍ ይላል ሲባል፤ ከኮሌጅነትም ዝቅ እንዲል በትግራይ ክልል አስተዳደር አማካኝነት ጫና እየበዛበት ነው።
በእነዚህ እና በመሳሰሉት ጫናዎች ምክንያት የአካባቢው ነዋሪ የቁጣ ተቃውሞውን በማሰማት ላይ ይገኛል። በመሆኑም በትላንቱ እለት የመንግስት ሰራተኞች ወደ ስራ ባለመግባት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። የኮሌጁ ተማሪዎች እና የባጃጅ ሹፌሮች ጭምር ይህንን የስራ ማቆም ተቀላቅለዋል። ብሶታቸውን በነጻነት ለመግለጽም በሚቀጥለው እሁድ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጥያቄ ማቅረባቸውን ለኢ.ኤም.ኤፍ የደረሰው ዘገባ ያመለክታል።
ባለፈው ወር የፌዴራል ቴክኒክ እና ሙያ ኤጀንሲ ለክልሉ የጻፈውን ደብዳቤ ከዚህ ቀጥሎ ለህትመት አብቅተነዋል።
tigray mayechew1
tigray mayechew2

No comments:

Post a Comment

wanted officials