ሰመሐል ወለደች
የሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ የመጀመሪያ ልጅ የሆነችው ሰመሐል መለስ ልጅ በሰላም መገላገሏን ምንጮች አስታወቁ። ሰመሐል ከወለደች በኋላ እናትዋ አዜብ መስፍን « አዋረድሽኝ» በማለት ከቤት እንዳትወጣ በማድረጋቸው በአሁኑ ወቅት ሰመሐል በፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ መኖሪያ ቤት እንደምትገኝ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። ሰመሐል ማታ ማታ ሲያስለቅሳት የነበረው መፀነሷ እንደነበረና ለእናትዋም ሳትናገር መቆየትዋ ታውቋል። “ሰመሐል” በኤርትራ ውስጥ የሚበቅል ሽታ ያለው ቅጠል ሲሆን በበአል ቀናት ይህን ቅጠል ይነሰነሳል። ለማንኛውም ሰመሐል እንኳን በሰላም ተገላገልሽ። ..የአቶ መለስ የቅርብ ታማኝና ወዳጅ የሆኑት ፕ/ር እንድርያስ መኖሪያ ቤት ሳር ቤት አካባቢ ይገኛል። ከቪላው ደጃፍ አንድ ትልቅ ግራር አለ። ከስሩ አንድ ነጭ አህያ ሁሌም ታስራ ስትግጥ ትታይ ነበር። አሁን ትኑር አትኑር አላውቅም። ነጯ አህያ ከ12 አመት በላይ ነበረች። ለፕሮፌሰሩ የቅርብ ወዳጅ የነበረው እስኬ ጓደኛዬን “አህያዋ ምንድናት?” ስል ደጋግሜ ጠይቄዋለሁ። እሱም እንድርያስን ሲጠይቅ መልስ ሰጥተውት አያውቁም። ነጭ አህያ ምን ትሆን?…በነገራችን ላይ ..ማራዘሚያ ከሚወስዱት ባለስልጣናት አንዱ ፕ/ር እንድርያስ እሸቴ ናቸው።
እየሩሳሌም አርአያ