Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, August 29, 2014

ኢትዮጵያ አስገዳጁን ውል ከግብጽና ሱዳን ጋር ተፈራረመች

ኢትዮጵያ አስገዳጁን ውል ከግብጽና ሱዳን ጋር ተፈራረመች

ኢሳት ዜና :-የግብጽ ጋዜጦች እንደዘገቡት ኢትዮጵያ ለወራት ውድቅ ስታደርገው የነበረውን ስምምነት ከግብጽ ጋር
ተፈራርማለች። አዲሱ ስምምነት የአባይ ግድብ ግንባታ በውጭ አገር ገለልተኛ አጥኚዎች እንዲጠናና ኢትዮጵያም የጥናቱን ውጤት እንድታከብር የሚያስገድድ ነው።
በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ሲደራደሩ የቆዩት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ ከወራት በፊት ሱዳን ላይ ተካሂዶ በነበረው የሰላም ስምምነት ላይ
ግብጽ ግድቡ በውጭ አገር ባለሙያዎች እንዲጠና ያቀረበቸውን አጀንዳ ውድቅ ማድረጓን ገልጸው ነበር። ኢትዮጰያ ግድቡ ከመጀመሩ በፊት በቂ ጥናት እንደተካሄደበት
እንዲሁም ገለልተኛ አካል አጥንቶ ችግር እንሌለበት መግለጹን ስታስረዳ ቆይታለች። ይሁን እንጅ ሰሞኑን በተደረገው ውይይት ኢትዮጵያ በፊት የያዘቸውን አቋም ቀይራ
በግብጽ አቋም በመስማማት አስገዳጅ ውል ፈርማለች። ውሉ የግድቡ ግንባታ ሳይቋረጥ እንዲካሄድ የሚጠይቅ ሲሆን፣ አዲሱ አጥኚ ቡድን ግድቡ በግብጽ ላይ ችግር ያስከትላል
ብሎ ካመነ ኢትዮጵያ የግድቡን ዲዛይን ለመቀየር ትገደዳለች።
ኢትዮጵያን ይህን አስገዳጅ ውል ለመፈረም ምን እንዳስገደዳት በግልጽ የታወቀ ነገር የለም።

No comments:

Post a Comment

wanted officials