የአቶ ተፈራ ዋልዋ ባለቤት በጥፊ ተመተዋል
ስለ ጉዳዩ በወቅቱ “ሪፖርተር” ጋዜጣ የአቶ ተፈራ ዋልዋ ባለቤት ወ/ሮ አይኔ ከማዕከላዊ ፖሊሶች ጋር በፈጠሩት አለመግባባት ለሰዓታት ታስረው ተፈቱ በማለት በደፈናው መዘገቡን ያስታወሰው የድህንነት አባል በጥፊ መመታታቸውን ደፍሮ ሊዘግብ እንዳልቻለ ገልፆዋል። በአጋጣሚ ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር ስብሰባ ላይ የነበሩት አቶ ተፈራ ዋልዋ ስልክ ተደውሎ በባለቤታቸው ላይ የተፈጠረው ሲነገራቸው በቁጣ ስብሰባውን አቋርጠው እንደወጡ አያይዞ አስታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከየመን ተይዘው ኢትዮጵያ የተወሰዱት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ እንደሌሉ ታማኝ ምንጮች አረጋግጠዋል። አቶ አንዳርጋቸው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ህንጻ ቢሮ ለአንድ ቀን በእህታቸው አይኔ ፅጌ መጐብኘታቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ ስለመገናኘታቸውም ሆነ ስለአንዳርጋቸው ከማንም ጋር ምንም አይነት ንግግር እንዳያካሂዱ በነግርማይ ማንጁስ ለወ/ሮ አይኔ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው አጋልጠዋል። ወ/ሮ አይኔ ከሌላው ጊዜ በተለይ ዝምታና ገለልተኛነትን እንደመረጡ ምንጮቹ አያይዘው ገለፀዋል።
No comments:
Post a Comment