ኢትዮ ቴሌኮም ስራተኞችና አስተዳደሮች ፂማቸውን እንዳያሳድጉ ተከለከለ!
ይህ ኢሥላምንና ሙስሊሞችን የማክሰም ዘምቻ ካለፈው ወርሃ ሃምሌ 2003 ዐ.ል ጀምሮ ሙስሊም ሙህራንን፣ የፕሪፓራቶሪ(Preparatory) ፤ የሃይስኩል(Highschool)፣ የዩኒቨርስቲ(universities) ተማሪዎችን፣ ዳዒዎችን፣ ኢማሞችና ሙዓዚኖችን ኢላማ በማድረግ አሥከፊና አስነዋሪ እርምጃዎችን ወስዷል እየወሰውደም ይገኛል።
ምንጮቻችን እንደገለፁት ያለፈው ሳምንት አመታዊ የስራ ክንውኖችንና ቀጣይ የማሻሻያ ግምገማና ውይይት የመንግስት ትልቁ ተቋም የሆነው የኢትዮጲያ ቴሌ ኮሚኒኬሽን ኮርፔሬሽን(ኢትዮ ቴሌኮም) ሰራተኞችና ጨምሮ የመስሪያ ቤቱ ትልልቅ ባለስልጣናት የተሳተፉበት ስብሰባ መካሄዱን የገለፁ ሲሆን በስብሰባውም ላይ በቴሌኮሙ ቀጣይ መሻሻልና መደራጀት ያለባቸው አሰራሮች ከስራተኞቹ የቀረቡ ሲሆን መሻሻል እንዳላባቸውና ከውጪ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማምጣት የተቀላጠፈ አስራር በያዝነው አዲስ አመት አሻሽለን እንቀጥላለን በማለት ውይይቱ ተጠናቋል።
ይሁንና አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪና የኮሙዩኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በአ/ቶ ደብረ ፂዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የኢትዮጲያ ቴሌኮሚኒኬሽን ኮርፖሬሽን(ኢትዮ ቴሌኮም) ካለፈው ከተቋጨውና በውይይታቸው ላይ ከተነሳው አጀንዳ ውጪ ሙስሊም ሰራተኞችን በግልፅ የሚያሸማቅቅና በግልፅ ሙስሊም የቴሌኮሙን ሰራተኞችን ኢላማ ያደረገ ህገ ደንብ እንደወጣ የአዛን አንቲ-አህባሽ የመረጃ መረብ ምንጮች ገልፀዋል።
በህገ ደንቡ ላይ ማንኛውም የኮርፖሬሽኑ ሰራተኞችና አስተዳደር ፂሙን ማሳደግ እንደማይችል፣ ሱሪውን ማሳጠር እንደማይችል፣ ለሴቶች ,ደግሞ አባያ፤ጅልባብ፤ኒቃብ፣ አባያ መልበስ እንደማይችሉ፤ጉርድ ,ቀሚስ ና ሸሚዝ እንዲያደርጉ የተገለፀ ሲሆን ሙስሊሞችን ብቻ አላማ ያላደረገ ለማስመሰል በደንቡ ላይ ፀጉር ማሳደግ፣ ፀጉር መፈረዝ፣ ሲኪኒ ሱሪ መልበስ እንደማይችል …ወ.ዘ.ተ እንደተገለፀ ታውቋል።
የወጣው ህገ ደንብም ከጥቅምት ወር 2007 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ምንጮች አያይዘው ዘግበዋል።
No comments:
Post a Comment