Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, September 10, 2014

የዘ-ሐበሻ አንባቢያን የዓመቱ ምርጥ ሰው መምህር አብርሃ ደስታ ሆነ

የዘ-ሐበሻ አንባቢያን የዓመቱ ምርጥ ሰው መምህር አብርሃ ደስታ ሆነ (የ36ቱን እጩዎች ዝርዝር ይዘናል)

  • 597
     
    Share
person of the year
(ዘ-ሐበሻ) እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን። የዘ-ሐበሻ አንባቢያን ከሦስት ዓመት በፊት መምህር የኔሰው ገብሬን የዓመቱ ምርጥ ሰው ሲሉ በ2004 ዓ.ም መርጠው ነበር። ቀጠሉና በ2005 ዓ.ም የዓመቱ ምርጥ ሰው አድርገው የሰየሙት እድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት የሚገኘውውን አንዷለም አራጌን ነበር። ዘንድሮም እንዲሁ ዘ-ሐበሻ ለአንባቢዎቿ የአመቱን ምርጥ ሰው ምረጡ በሚል ባቀረበችው መጠይቅ መሰረት የተለያዩ ምርጥ ታጋይ ኢትዮጵያዉያን የአንባቢዎቻችንን ድምጽ አግኝተዋል። በሺዎች የሚቆጠሩ መራጮች በሰጡት ድምጽ መሰረት ለአመቱ ምርጥ ሰውነት የታጩት የሚከተሉት ናቸው።
1ኛ. ቴዲ አፍሮ
2ኛ. አበበ ገላው
3ኛ. ታማኝ በየነ
4ኛ. አብርሃ ደስታ
5ኛ. ጥሩነሽ ዲባባ
6ኛ. መሠረት ደፋር
7ኛ. ሔኖክ ዓለማየሁ
8ኛ. አንዷአለም አራጌ
9ኛ. እስክንድር ነጋ
10ኛ. አንዳርጋቸው ጽጌ
11ኛ. ሌንጮ ለታ
13ኛ. ጄነራል ከማል ገልቹ
14ኛ. ታጋይ ሞላ አስገዶም
15ኛ. ርዕዮት ዓለሙ
16ኛ. አቡበከር አህመድ
17ኛ. ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ
18ኛ. ኃይለማርያም ደሳለኝ
19ኛ. ካፒቴን ኃይለመድህን አበራ
20ኛ. ሊያ ከበደ
21ኛ. የሺዋስ አሰፋ
22ኛ. በቀለ ገርባ
23ና ኦልባና ሌሊሳ
24ኛ. ፕ/ር ተካልኝ ማሞ
25ኛ. ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
26ኛ. ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም
27ኛ. ኢንጂነር ተስፋሁን ጨመዳ (በወህኒ ቤት ያረፉ)
28ኛ. ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት
29ኛ. ዶ/ር መረራ ጉዲና
30ኛ. ሃብታሙ አያሌው
31ኛ. የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምዕመናን
32ኛ. ኦባንግ ሜቶ
33ኛ. ቴዎድሮስ አድሃኖም
34ኛ. በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵዮጵያውያን
35ኛ. ጃዋር መሐመድ
36ኛ. እና ሌሎችም
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ገልሰቦች ድምጽ ያግኙ ኢትዮጵያውያን ሲሆኖ ክነዚህ ውስጥ 624 ድምጾችን ያገኘው ታዋቂው ታጋይና በአሁኑ ወቅት በእስር ቤት የሚገኘው አብርሃ ደስታ ነው። ከሱ በመቀጠል ተቀራራቢ ድምጽ ያገኘው ታጋይ በወያኔ እስር ቤት የሚገኘው አንዳርጋቸው ጽጌ ነው። 601 ድምጾችን ያገኘው አንዳርጋቸው ጽጌ በቀጣይ ሲቀመጥ 534 የሚሆን ድምጽ ያገኘው ደግሞ ታጋይ ሃብታሙ አያሌው ነው። የዓመቱ ምርጥ ዘፋኝ የሚለውን የአንባቢዎቻችንን ክብር ያገኘው ቴዲ አፍሮ ሲሆን 369 ድምጾችን አግኝቶ ከሌሎች አርቲድቶች የተለየ ሆኗል።
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/34465

-- Ze-Habesha Website

No comments:

Post a Comment

wanted officials