የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ
ከሰሞኑ በተካሄደው ስልጠና እናተያያዥ ጉዳዮች ከመምህራን ጋር መስማማት ያልቻልው ገዢው ፓርቲ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተማዎቸ በመምህርነት ሙያ እያገለገሉ የሚገኙ የተለያዩ ወጣት መምህራንን ስልጠናው በተሳካ ምክንያት እንዳይካሄድ እንቅፋት በመሆን እንዲሁም በትምህርት ቤቶቸ ውስጥ ድብቅ አጀንዳ ይዛቹህ ስትንቅሳቅሱ ተገኝታቹሀል በሚል ምክንያት የተነሳ ህወሀት መራሹ መንግስት የሚከተሉትን መምህራን ከሚሰሩበት ትምህርት ቤት ያለፍላጎታችው ተነስተው ወደ ገጠራማ ስፍራዎች እንዲመደቡ ተደርገዋል፡፡ እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ ባገኘው መረጃ መሰረት በግዴታ ዝውውር የተሰጣቸው መምህራን የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. መ/ር ይማም ሐሰን
2. መ/ር ሙለታ ዲንቃ
3. መ/ር ኤርሚያስ ተገኝ
4. መ/ር ሐይለ አምላክ ይገዙ
5. መ/ር ደምስ ግዛቸው
6. መ/ር አንዳርጋቸው ምህረቴ
7. መ/ር አንተነህ ንጉሱ
8. መ/ር ይስሀቅ ጉደታ
9. መ/ር መላኩ አበበ
10. መ/ር ዮሐንስ ካሳሁን
11. መ/ር ዳዊት የሺጥላ
12. መ/ር ዘሪሁን አላምረው ሲሆኑ ከትላንትናው እለት ማለትም 19/01/2007 ዓ.ም ጀምሮ ከስራ ገበታቸው ያለፍቃዳቸው መነሳታቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በ2004 ዓ.ም የደመወዝ ጭማሪን ተከትሎ በተነሳ ተቃውሞ በተመሳሳይ መንገድ በርካታ መምህራን ከስራ የመባረር እና ራቅ ወዳሉ ስፍራዎች መመደባቸው ይታወሳል