Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, January 13, 2015

በጀርመን ፍራንክ ፈርት ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

demonstration germeny
በዳዊት መላኩ
በጀርመን ፍራንክ ፈርት በዛሬው ዕለት ማለትም 12/01/2015 እ.ኤ.አ ከጠዋቱ 11፡00 ሰዕት ጀምሮ መነሻውን የዶቼ ባንክ ዋና ጽ/ቤት ከሚገኝበት አድርጎ መድረሻውን የወያኔው ቆንስላ ጽ/ቤት ያደረገ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ፡፡
በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሰልፉ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን የዶቼ ባንክ ቦርድ ለወያኔ መንግስት ሊሰጥ ያሰበውን የሶቨርንግ ቦንድ ሽያጭ እንዲያቆም የሚተይቁ የተለያዬ መፈክሮችን ያሰሙ ሲሆን ለበርካታ ነዋሪዎች ይህን በሚመለከት በራሪ ወረቀቶችን አድለዋል፡፡ሰልፈኞች ያሰሟ ቸው ከነበሩ መፈክሮች መካከል፡- ጀርመን የዜጎችን መፈናቀል አትደግፊ፤የመሬት ወረራን እንቃወማለን፤ ጀርመን ላንባገነን መንግስት የሚትሰጪውን ድጋፍ አቁሚ፤የፖለቲካ እስረኞች ያፈቱ የሚል ይገኝበታል፡፡ በተጨማሪም ሰልፈኞቹ የነጻነት ታጋዩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አስመልክቶ በፍራንክፈርት የእንግሊዝ ኢምባሲ ቆንስላ ጽ/ቤት ፊት ለፊት የተለያዩ መፈክሮችን ያሰሙ ሲሆን እንግሊዝ ዜጋዋ የሚፈታበትን መንገድ አጠናክራ እንድትጠይቅ አሳስበዋል፡፡በተወካያቸው በኩልም ደብዳቤ አስገብተዋል፡፡በመጨረሻም ሰልፈኞቹ ጉዟቸውን ወደ ኢትዮጵያ ኢምባሲ በማምራት የፖሊተካ አስረኞች ይፈቱ፤ ነጻነት እንፈልጋለን፤ፍትህ ለፖለቲካ እሰረኞች፤ፍትህ ለሞስሊም ተወካዮች ፍትህ ለጋዜጠኞች፤ወያኔ ስልጣኑን ይልቀቅ፤መንግስት ዜጎችን ማሸበሩን ያቁም ወዘተ የመሳሰሉ መፈክሮችን ያሰሙ ሲሆን ባለ አንባሸውን የወያኔ ሰንደቅ አላማ አውርደው በትክክለኛው የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ለመተካት የተደረገው ጥረት በፖሊሶች ከፍተኛ ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡


No comments:

Post a Comment

wanted officials